Montag, 31. März 2014

ከፈለክ አንብበው፤ ድምጽ ካልታሰበም ይወጣል እና



ከፈለክ አንብበው፤ ድምጽ ካልታሰበም ይወጣል እና

ኢትዮጲያ ውስጥ ትልቁ ችግራችን በብዛት እንጂ በጥራት አናምንም፡፡ ይህም ሁኔታ በቤተክርስቲያን አመርቂ ስራ ሊሰራ አልቻለም፡፡ ከቶም ለእግዚአብሄር የሚቀርቡ ሰዎች የተገለሉበት ወቅት ላይ ደርሰናል፡፡ እግዚአብሄር ኢትዮጲያን ብዙ ጊዜ በመጽሀፍ ቅዱስ ላይም ቢጠራትም መከራችን ግን እንዲሕ በቀላሉ የሚቁዋጭ አልሆነም፡፡ እግዚአብሄር የመንፈስ ጉዳይ ሆኖ ሳለ ግን ቤተክርስቲያን እያተኮረች ያለችው በስጋ የምንከብርበት ነገር ላይ እየሆነ መጥቶአል፡፡ እኩል በልቶ ባማይታደርበት አገር ስለ ስጋ ጸጋ ማውራት ቢከብድም ይሁን ብለን የተቀበልነው ነበርን፡፡ ግን የሀብቱ ሁኔታ ሊመጣጠን አልቻለም፡፡ በሀብታም እና በደሃ መካከል ያለው ሁኔታ እንደኢሮፕ አይደለም፡፡ ኢትዮጲያ የተራበው ደመውዝ ማገኘቱ ይቅርእና፤ ደመወዝ ስለመኖሩም የማያውቅ ብዙ ነው፤ ደመወዝ የተያያዘው ከስራ ጋር ነውእና፡፡ ብዙው በእግዚአብሄር ጥበብ ብቻ የሚኖር መሆኑ ይታወቃል፡፡ ሀብታም ለምን ሀብታም ሆነ አልልም፡፡ ግን የሚራበው እንዴት ይሁን ነው ጥያቄው? የተራበውን እጠገበው አጠገብ አስቀምጠሕ የእግዚአብሄርን ቀን ጠብቅ የሚል ክርስቲያን ምንአይነት ክርስቲያን እንደሆነ እራሱን ይመርምር፡፡ በውነቱ ሰው ሀብታም  የሚሆነው እግዚአብሄር መርጦት ነው የሚለውን፤ የሱን ጽድቁን ቢነገረኝ ደስ ይለኛል፡፡ ሰይጣንም የመረጠው ሰው፤ መቼ በአለም ደሃ ሆነእና፡፡ ጭራሽ ባይበልጥ? የተራበው ደግሞ ሀጢያቱ አለማመኑ ነው የሚለኝ እርሱ አምኖ ያመጣውን ሳይ ነው፡፡  ታዲያ የእግዚአብሄር ፍቅር በአለም ሀብት የሚወሰን ከሆነ እና የስጦታ ነገር ከሆነ ሰይጣንስ ይሰጥ የለምእን? ከእንግዲሕ ወንጌልን ማስረዳት የሚቻለው በኑሮሕ እና በባህሪ መለወጥ አሳይተህ  እንጂ፤ መጽሃፉ ላይ የሚነገረውን ደጋግመህ ካለባህሪ መለወጥ በመናገር አይደለም፡፡ እንግዲህ ኢሕአዴግ ከገባ 20 አመት ሆኖታል፡፡ 20 አመት ሙሉ ወንጌል በነጻነት ሲሰራጭ ቆይቶአል፡፡ ኢሕአዴግ ጠረፍ እስከጠረፍ ወንጌልን ለሚሰብኩ ሁሉ ነጻ አድርጎታል፡፡ ግን የተማርነው ያደረገን እራሱ ኢሕአዴግ የተባለውን እንድነፈራ እና እንድንሽቆጠቆጥለት እንጂ እግዚአብሄርን አይደለም፡፡ ብዙ ሰው ስለወንጌል ሰምቶአል፡፡ ግን አሁን ብዛቱ ሳይሆን ጥራቱ ላይ ችግር እንዳለ ለእግዚአብሄር ብቻ ሳይሆን ለአለም እንኩዋን ስውር ሊሆን አልቻለም፡፡  ኢትዮጲያ ጥሩ ግዜ እንደሚመጣላት ትንቢት ተነግሮላታል ቢባልም፤ መነገሩ ቀኑን ያሳጥረዋል ማለት አይደለም፡፡ እና ግን ዛሬ ኢትዮጲያ ተለውጣ ብናይ ደስ ይለን ነበር፡፡ ይህ ተስፋ ግን ከቀን ወደቀን እየጨለመ ሄድዋል፡፡ ከመቼውም በላይም በንዋይ ውዴታ ባህር ውስጥ ገብተን መዋኘት እና መውጣትም የተሳነን ክርስቲያኖች እየሆንን ነው፡፡ አንዳንዱም ጸሎቱ ከጥቅሙ ጋር በተያያዘ እንጂ ከምድራችን መለወጥ ጋር የተያያዘ አይደለም፡፡ የመንግስትን እድሜ መርዘም የሚመኘው ከራሱ በመነሳት እንጂ ከእግዚአብሄር ድምጽ አይደለም፡፡ ለሚያምኑ ሁሉ መክበር በመንፈስ እንጂ በስጋ እንዳልሆነ ለማንም ለገባው ግልጽ ነበር፡፡ ዛሬ ግን ስለ ንዋይ ጸጋ የማያወራ የከሰረ ክርስቲያን ተብሎአል፡፡ ይህ ከክርስቶስ መልእክት ጋር በጣም ይጋጫል፡፡ ማውራት ያለብን ስለምድራችን መባረክ ነበር፡፡ መስራትም ያለብን ስለአገራችን ህዝብ ነበር፡፡ ዛሬ ግን ከፋፍለነዋል፡፡ ግልጥ ለማድረግ፤ ሕዝብ በሚለማመደው ልምምድ በዘር ጉዳይ፤ በኑሮው ውድነት ጉዳይ እና በተለያየው ነገር ላይ ኢሕአዴግን ጥፋተኛ አድርጎ ሕዝብ አፍጥጦበታል፡፡ እኛስ ወንጌልን አውቀን ስናጠፋ እግዚአብሄር ሳይሆን ሰውስ ምን ይለኝ ይሆን ብለን ተየቅን? እውን የተራበ ፔንጤ የለምእን? እውን ባለው ልዩነት እምነቱ ፈተና ላይ የወደቀበት ክርስቲያን የለም እን?
 እንግዲሕ እግዚአብሄር ይርዳኝ እና ሀሳቤን ግልጽ ላድርገው፡፡ ከኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ሀይማኖት እጅግ ብዙ ሰው ወደ ጴንጤ በወንጌል መማረክ የተነሳ ሄዶአል፡፡ ተስፋውን የሚፈልግ ሰው በወንጌል እንደሚረካ አንድእና ሁለት የለውም፡፡ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያዋ ሆና ሳለች ግን በወንጌል ትምህርት አሰጣጥ በኩል ዘመኑን መከተል እና ወጣቱንም በሚገባው መንገድ ለመሳብ የምታደርገው ጥረት በሁሉም አካባቢ ያልተስተካከለ በመሆኑ ብዙ ሰው ወደ ፔንጤ መዞሩ የታወቀ ነው፡፡ እንዳውም ከሌላ ሀይማኖት ወይም ከማያምን ወገን ወደፔንጤ ከሚመጣው ይልቅ ከኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እየፈለሰ የሚመጣው በእጅግ ይበልጣል፡፡ ወንጌልን መስበክ የቀለለው ድሮም ክርስቲያን ለነበሩት እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ከኦርቶዶክስ የሚፈልሰው የምትሀት ጉዳይ ሳይሆን፤ የነፍስ ጥሜት ጉዳይ ነው፡፡ ነፍሳችን ወንጌል ነው ምግቡዋ፡፡ አፈጣጠሩዋም ከዛው ነበር፡፡ ሌላው ከኦርቶዶክስ የምእመናን ወደ ፔንጤ መሸሽ  ወይም በቤት ውስጥ ተደብቆ መቆየት ያመጣው ደግሞ፤ የኦርቶዶክስ ለሁለት መሰንጠቅ ያመጣው እሰጥ አገባ ነው፡፡ ይህ በምእመናን መካከል አለመተማመንም ፈጥሮአል፡፡ ይህን ከልምድ ልናገር የምንችል ሰዎች አለን፡፡ በሁሉም ያለው ችግር እግዚአብሄርን ከመከተል ስርአትን የሙጥኝ በማለታችን ጉዳት በቤተክርስቲያን ውስጥ መጥቶአል፡፡ የተቃዋሚ ነህ የደጋፊ የሚለው ንግግር ሁላችንንም ያስደነግጣል፡፡ እምነት ባወከው ብቻ የምትኖረው አይደለም፡፡ ሁልግዜ አዲስ መመገብ አለብህ፡፡ ልብ ካልን እምነት ግንኙነቱ ከመንፈስ ጋር እንጂ ከስጋ ጋር ባለመሆኑ፤ እምነታችን ለስጋ በሚያስፈልገው ምግብ የሚኖር አይደለም፡፡ እኛ ሁልግዜ ስለዚህ አለም ባሰብን ቁጥር መንፈሳችን እጅግ ያዝናል፡፡ ለእሱ የሚሆን ምግብ ስለማናቀርብለት ይሳሳል ይከሳል፡፡ ይሞታልም፡፡ መንፈስህን ገለህ ግን በውስጥህ ተሸክመሕ ትሄዳለሕ፡፡ አሁን ስለመንፈስ አስፈላጊነት ከገባህ ዛሬውኑ ከሞተበት ለማስነሳት ትችላለህ፡፡ ይህ እግዚአብሄር ለሁሉ የሰጠው ስጦታ ነው፡፡ ንስሀ ትገባለሕ፤ አዎ የሞተው መንፈስህ አራስ ሆኖ ይወለዳል፡፡ በቃ ዳግም ይወለዳል ማለት ነው፡፡ ይሁንና ይህ በቂ አይደለም፡፡ መልሶ እንዳይሞት የሚገባውን መንፈሳዊ ምግብ መስጠት አለብህ፡፡ እንግዲሕ ይህ ነው ሰው ነፍሱ ወደእግዚአብሄር ያላት ጥሜት እንጂ ከአንዱ ወደአንዱ የሚሮጠው ሌላውን ስለካደ አይደለም፡፡ የሚካደው ሰይጣን ነው እንጂ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አይደለችም የምትካደው፡፡ ግን ስለመንፈስ ከተረዳን የነፍሳችን ጥሜት ወንጌል ፍለጋ እንድንሄድ የሚያስገድዱን ነገሮች አሉ፡፡ ይህ የምትኖረው እንደተሰጠህ ነው፡፡ እኔ ወደ ፔንጤ ስሄድ የወንጌል ጥሜቴ እንጂ ገንዘብ ተከፍሎኝ ወይም ሰው ሰብኮኛ አይደለም፡፡ አንዳኑዱ ብዙ መጨናነቅ ይደርስበት እና ወንጌልን ሲሰማ በውነት ይድናል፡፡ ወንጌል መድሀኒት ነው፡፡ ሰካራም የነበረው ተደባዳቢ የነበረው ሁሉ ወንጌልን ሲሰማ የተለዬ ሰው ይሆናል፡፡ ክርስቶስ መዳኒት የሚሻ ብሎአል፡፡ አዎ መድሀኒት ፍለጋ ይኬዳል፡፡ ነፍሳችንን ለማዳን ወደወንጌል ሄደናል፡፡
አሁን እኔ ወንጌልን ልሰብክ አይደለም፡፡ እኔ ለዚህ ነገር የሚገባው ጸጋው የለኝም፡፡ የምመሰክረው ግን ለእኔ ህይወት ወንጌል ወሳኝ እንደሆነ እና እውነትን መረዳት መቻሌ ነው፡፡ በክርስቶስ ፍቅር እንዳለ አውቃለሁ፡፡ ዘወትር ስለክርስቶስ ስሰማ ልቤ የተለየ እርካታ እና ደስታ ያገኛል፡፡ ሀብት አገኘሽ ወይ አትበሉኝ፡፡ እንዳውም የዚህ አለም ሀብቴ እየቀነሰ የሄደው ክርስቶስን ካወኩ በሁዋላ ነው፡፡ ግን ያገኘሁት ሀበት ከዚህ አለም ሀብት ለየት ያለ ነው፡፡ በቃ ነውር የሆኑ ነገሮችን ሁሉ እንድጠየፍ እንዳልስገበገብ በልቤ ወስጥ ያስቀመጠው ነገር ያለ ይመስለኛል፡፡ ወገኔ ያሳዝነኛል፡፡ ያስለቅሰኛል፡፡ ይህቺን የመሰለች ምድር ኢትዮጲያ ልጆቹዋ ሲንከራተቱ ልቤ ይሰበራል፡፡ ምሁሮቻችን ተምረው እንዳልተማሩ ሲሆኑ አልያም ለእኛ ሳይሆኑ ለሌላ አገር በረከት ሲሆኑሣይ፤ ጌታ ሆይ እላለሁ፡፡ ፖለቲከኞቻችን ሁሉ መስማማት ሲያቅታቸው አስታራቂ ለመሆን ይቃጣኛል፡፡ ከፍቅሬ የተነሳ አወናባጅ ፖለቲከኛ መስዬ ወዲህ ወዲያ እላለሁ፡፡  ለእኔ መንፈሴ ከስጋዬ በልጦአል እና ከክርስቶስ በተሰጠኝ ነገር እርካታን አገኝቻለሁ፡፡ ሀብቴ ሰማያዊ አለም እንጂ ይህ አለም ከቶም አይሆንም፡፡ የመጨረሻው የሚያዋርድህ ወርቅ አለመልበስህ መኪና አለመንዳትህ ሳይሆን ሆድህ ሲርበው ነው፡፡  ለምነህ የማታገኝበት፤ ሰርተህ የማትጠቀምበት አገር እራብ ያዋርዳል፡፡ ለስጋዬ የእለት እንጀራ ይበቃኛል፡፡ ሆድ ግዜ የሚሰጥ ነገር አይደለም፡፡ ኢንቬስት አድርገህ ሰርተህ የማትጨርሰው ሆድ ተሸክመሃል፡፡ እሱ አዋራጅ ነው፡፡ እየሱስም የእለት እንጀራችሁን ለምኑ ያለው፤ ከዚህ ሌላው ሁሉ ቢቀርም የማይጎዳ ነው፡፡ በውነት አይጎዳም፡፡ መኪና ባይኖርህ ምንትሆናለሕ? እሚወልድ ገንዘብ ባይኖርህ ምን ትሆናለሕ? በቃኝ ካልክ በሆድህ ይብቃህ ወዳጀ፡፡ ካልሆነ አለም እና መሬት በልተው የማይጠግቡ ናቸው፡፡  ሌላው ደግሞ „ጥረህ ግረሕ ብላ“ ያለውን ፍርድ እና እርግማን ስላለ፤ ካለፋሁ እንደማላገኝ አድርጌ እራሴን ስላሳመንኩት የላቤን እንዲበቃኝ እጸልያለሁ፡፡ ግን ወደተነሳሁበት ልመለስ እና ከየትም መጣ ከየትም የፔንጤ ምእመናን በእጅጉ በዝቶአል፡፡ እኔም እዛ ውስጥ ነኝ፡፡ ግን ምድራችን ደግሞ ከመቸውም በበለጠ፤ ሞራል ለለው ነገር ብዙው ተጋልጦአል፡፡ ሙስናው የሚያስመርር እና በምድሪቱ ላይ መርገምን የሚጠራ ሆኖአል፡፡ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ሴት አዳሪው በዝቶአል፣ ህጻናት ጎዳና ላይ ወጥቶአል፡፡ የተስፋውም ሆነ የትንቢቱ ነገር ጭላንጭል ማሳየት አቅቶታል፡፡  ታዲያ ቤተክርስቲያን ብዙ ሚሊዬን ክርስቲያን ከያዘች፤ ምነው ምድሪቱን የሚታደግ አንድ ሙሴ ወይ አንድ ዳዊት አልያም ዮሴፍ እንዴት ይጠፋል? እኛ ሁሉ ለወንጌል ከቆምን ያለው መንግስት መልካም ሰርቶ እንዲያልፍ ባህሪው እንዲስተካከል ምነው ጸሎት አልረዳውም ? ውድ የቤተክርስቲያን ሰዎች መጥፎውንም ስንቃወም የታየነው እንደፖለቲካ ሰው ሆኖ ስንሰደድ ቤተክርስቲያን ለምንስ ዝም ትላለች፡፡ በስነምግባር ብልሹዎች ሰንረበሽ ቤተክርስቲያን ምነው ከመንግስታቶች ጋር ቀርበው ወንጌልም ስራ አለው ብለው ያልተፋጠጡት፡፡ ለመሆኑስ መንፈስ ሊታገድ እንደማይችል ለማስረዳት ምንነው የቤተክርስቲያን አፍ ተዘጋ፡፡ ሰው ዲሞክራሲ አለ ተብሎ ተከርቸም ሲወርድ ምነው አንድ የቤተክርስቲያን ሰው ጠፋ ሀግ የሚለው፡፡ አልገባኝም፡፡ ግን ዛሬ ፍርሀት አለኝ፡፡ እሱም የሚቀጣው አውቆ ያጠፋ ነውእና፡፡ የሚቀጣው አስመሳዩ ነውእና፡፡ ወዳጄ ሆይ ንጉሱ ሳዖልን ከረሳህ፤ በእግዚአብሄር የተመረጠውን ዳዊትን እንዴትስ አውቃለሁ ትላለህ፡፡ ዳዊትንስ ካላወቅ ወንጌል ሲናገሩት ቀላል ሲፈጽሙት ከባድ ይሆንብሀል፡፡ በዘር ክፍፍል ባልነበረ ሁኔታ ምነው ዛሬ ወንጌል በይፋ ሲሰበክ መጣ፡፡ እውን እግዚአብሄር አይፈርድምእን? ወገኔ ሆይ ኢትዮጲያን አሳልፈህ ለክፉ እንዳትሰጣት ወደእግዚአብሄር ንስሀ ግባ፡፡ አንተም የከፋህ ወንጌል በእጁ የያዘ ሲያጠፋ ባየህ ቁጥር ከወንጌል ጋር ለምን ትታገላለህ፤ እግዚአብሄርስ ለሰው ስገዱ ብሎ ወንጌል ላይ አስፍሮላቼዋልእን? የኢትዮጲያ ህዝብ የማረፊያ ቀንህ አይዞሕ ይመጣል፡፡ ግን ቀኑ እንዲፋጠን የሰው ጀግና ከምትመኝ እጅህን ወደ ፈጣሪህ አንሳ፡፡  ከቶ ለእግዚአብሄር ምን የሚሳን ነገር አለ፡፡ ለቃሉስ የሚቀርቡ ደግሞም ወደንጉሶች የተላኩ ነበሩ፡፡ ግን የሚደፍረው መንፈስ እንጂ ስጋ አይደለም እና፤ ባስቀየምኩ በጌታዬ በእየሱስ ክርስቶስ ስም ይቅር በሉኝ፡፡ በሉ በቸር፡፡
ባዩሽ









Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen