Samstag, 29. März 2014

ጀርመን --------እንተዋወቅ



                                        ጀርመን --------እንተዋወቅ

በጀርመን አገር ሁሉም ሀብታም አይደለም፡፡ ግን የሚራብ የለም፡፡ እስራኤሎች በጀርመን ናዚ ዘመን በጀርመኖች በጣም አሰቃቂ ድርጊት ተፈጽሞባቸዋል፡፡ ዛሬ ግን ምህረት አድርገው አብረው በፍቅር እና በምክክር ይኖራሉ፡፡ በጀርመን አገር ሚሌኒየር አነስተኛ ገቢ ያለው ማህበረሰብ መካከል ይኖራል፡፡ የጀርመን ቤቶች አደገኛ አጥር የላቸውም፣ ዘበኛም የላቸውም፡፡ በጀርመን አገር ግብር የማይከፍል ሰው እንደከባድ ወንጀለኛ ሆኖ እስር ቤት ይወረወራል፡፡ በጀርመን አገር ሁሉም ሀይማኖቶች በነጻነት ይንቀሳቀሳሉ፡፡ ቄሶቹም አንዱ አንዱን ምሳሌ የሚያደርግ ትምህርት  አይሰጣጡም፡፡ በጀርመን አገር ትልቅ መስጊድ አለ ትልቅም ቤተክርስቲያን አለ፡፡ በጀርመን አገር ሀብታም በሚከፍለው ግብር ደሀ ጠግቦ በልቶ ያድራል፡፡ ደሀ ማለት በጀርመን አገር እንደልቡ አይሮፕላን ከፍሎ ከጀርመን ውጪ ለእረፍት የማይሄድ እነደማለት ነው፡፡በጀርመን አገር ከተለያየው የአለም ክፍል ሁሉ የመጣ  ዜጋ እኩል የሚኖርበት ሆኖአል፡፡ ዛሬ በጀርመን አገር ጥቁሮችም ፓለቲካ ውስጥ እየገቡ እየሰሩ ነው፡፡ እዚህ አገር የሚኖር ማንኛውም ዜጋ የሕክምን ኢንሹራንስ አለው፡፡ ጀርመን አገር ማንም እንደፈለገ ፖሊከኞችን መተቸት ይችላል መንቀፍ ይችላል፡፡ ጀርመን አገር የሞት ፍርድ የለም፡፡

ሌላው ጀርመን ትምህርት ቤት የወንጌል ትምህርት በቤተሰብ ፍቃድ እንደሳብጀክት ይሰጥ ስለነበር ብዙው ህዝብ ስለክርስቶስ ያውቃል፡፡ እንደእውነቱ ከሆነ ለሰብአዊ ነገር በጣም የተዘጋጀ የጀርመን ህዝብ ነው፡፡ ሀይማኖታቸው ፔንጤ እና ካቶሊክ ነው፡፡ ጀርመን አገር ምንም አይነት በሽታ ይዞት ቤተሰብ ቢያገለው መንግስት እና የሀይማኖት ድርጅቶች እንደካሪታስ ወይም ዲያኮኒ የሚባሉ ተረክበው ያስታሙሙታል ይረዱታል፡፡  እንዳውም እዚህ አገር በረከታቸው የተትረፈረፈው የተገለለውን የተጣለውን በማንሳታቸው ይሆናል ብዬ እገምታለሁ፡፡ በየቤቱ ምግቡ በጣም በረከት አለው፡፡ ትንሽ ብለን የሰራነው በጣም ይበዛል፡፡ ማለቂያ የለውም፡፡ ይበረክታል፡፡ ሁሉም እዚህ አገር የቴሌቪዥን ተጠቃሚ ነው ከፈለገ ማለት ነው፡፡


የጀርመን ህዝብ ስራ ይወዳል፡፡ በዚህ የተነሳም ባለሆቢ ነው፡፡ እያንዳንዱ ካለሆቢ አይንቀሳቀስም፡፡ መጠጥ የሚጠጣው በፕሮግራም ነው፡፡ ብዙውም የሚጠጣው ቢራ ነው፡፡ የውስኪ ባህል ብዙም የላቸውም፡፡ ጀርመን ካለቢራ ማለት ኢትዮጲያን ካለጠላእና ጠጅ እንደማለት ነው፡፡ ሰክሮ ብዙ የሚረብሽ የለም፡፡ አንድ ሰው ካልበረደው እራቁቱን ቢሄድ ዞሮ የሚያየው የለም፡፡
በጴንጤዎች ቤት አልኮሆል አይጠጣም፡፡ ፔንጤ ማለት ነጻ የሆነ ኢቫንጀሊስ ማለት ነው፡፡  ከፍተኛ ትምህርት ያለውም የለለውም አብሮ ይውላል፡፡ አንዱ አንዱን የመናቅ ሁኔታ በጭራሽ አይታይም፡፡ የጀርመን ህዝብ አብዛኛውን ግዜውን በስራ ስለሚያሳልፍ ሚስት እና ባል በሚለው ነገር ላይ ብዙም የቀናው አይደለም፡፡ቢሆንም ግን በጀርመን አገር ከስራ ቢዚ ከመሆን የተነሳ በጋዜጣ ወይም በቴሌቪዥን ወይም ለትዳር ማገናኛ በሆኑ ቢሮዎች ለትዳር የሚፈልጉትን መተዋወቅ ብልግና ሳይሆን እንደባህል እየሆነ እንዲመጣ የጊዜ እጥረት እያስገደዳቸው መጥቶአል፡፡ የሆሞሴክሹዋል ባህልን ሁሉ የተቀበለው እና የወደደው አይደለም፡፡ ግን እኔ ካልሆንኩ ስለሌላው ምንአገባኝ አይነት ነገር ይታያል፡፡

ይህም ሆኖ የኑሮው ውድነትን ሁሉም እየተናገረ ነው፡፡ ሰሞኑንም ሰራተኛው ሁሉ ለሰላማዊ ሰልፍ የደመወዝ ጭማሬ እየተነሳሳ ነው፡፡ ባለፈው የከተማው የትራንስፖርት ሰጪው አገልግሎት ክፍሉ የስራ ማቆም አድማ አድርጎ የደመወዝ ጭማሬ ጠይቆአል፡፡ ይህም በአገሩ ውስጥ የሰራ ቀውስ አምጥቶአል፡፡ ብዙው ሰው የከተማ ትራንስፖርት ተጠቃሚ በመሆኑ ስራ ሊሄድ ባለመቻሉ ብዙ ቀውስ ተፈጥሮ ውሎአል፡፡ መልስም ካላገኙ ይቀጥላል፡፡ በሚቀጥለውም የሉፍታንሳ ሰራተኛ እንዲሁ የስራ ማቆም አድማ ለደመወዝ ጭማሬ እንደሚያደርጉ ነው፡፡ የሚሰራ ሰው ስራ ማቆም አድማ ሲያደርግ ውጤት እንደሚያመጣ አይካድም፡፡  
ሰሞኑን በጀርመን አገር የሰራተኛው የደመወዝ ክፍያ መነሻ እስኬል እንዲጨምር ፖለቲከኞች ተሰባስበው ወስነዋል፡፡ ይህ ሲሆን ግን ሌላ ስጋትም አለ፡፡  ስጋቱም አሰሪው ክፍል የምግብ ዋጋ  ጭማሬ ሊያደርጉ እንደሚችሉ ነው፡፡ እንግዲሕ ጀርመን ይህን ይመስላል፡፡  

ይህም ሆኖ ግን እዚሕ አገር በልተው ጠጥተው በዲሞክራቲው ተጠቅመው የኖሩ የሶስተኛው አለም ስደተኞች ምን ህል ተለውጠው ይሆን? በዘር ክፍፍል ይሆኑ? ለተቃዋሚ ለገዢው ፓርቲ እያሉ ተከፋፍለው ይሆን? ተሰብስቦ ከማውራት የሆቢ ልምምድ ጀምረው ይሆን? ልብስ ከመቀያየር ሕሊናቸውን የሚያለብሰውን ስብእና ተምረው ይሆን? ክሪቲክ ጥቅሙን ተላምደውት ይሆን? ምንአልባት አገሩ ውስጥ የሚኖሩት ሳያውቁት ይሆን?  እንግዲህ ለእናንተው ልተወው፡፡ በቸር ልበላችሁ
ባዩሽ

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen