Sonntag, 13. Juli 2014

ህዝብ የሚከፍለው ግብር የአንድ ፓርቲ ሳይሆን የተቃዋሚውም ክፍል ነው፡፡



ህዝብ የሚከፍለው ግብር የአንድ ፓርቲ ሳይሆን የተቃዋሚውም ክፍል ነው፡፡
እኔ የማንኛውም ፖለቲካ አባልም ደጋፊም ሆኘ አላውቅም፡፡ ግን ዲሞክራሲን ምንነቱን እና ምቾቱን ስለማውቅ፤ ዲሞክራሲ እውን እንዲሆን እና፤ እረጅም ግዜ በምእራቡ አለም በመኖሬ የዲሞክራሲን ባህሪ ለማሳየት ብዙ ሞክሬአለሁ፡፡ በወሎ አካባቢ ያሉ በተለይ ደሴ ላይ ያሉ የኢሕአዴግ ባለስልጣናት እና የበለጠውም የአካባቢው ተወላጅ ጥረቴን እና ደግሞም በበጎ ያደረኩት እና የተናገርኩት ሁሉ እንደተቃዋሚ ታይቼ መንገላታቴን እና  በእጅ አዙር እንዳልሰራ መደረጌን ጠንቅቀው ያውቁታል፡፡ በእጅ አዙር ሲያንገላቱኝ የነበሩትን ሀሰተኞችም፤ እግዚአብሄር እንደሚበቀላቸው ጥርጥር የለውም፡፡ ስለዚህ ኢሕአዴግ ይህንን ስርአት አያውቅም ልል አልችልም፡፡ ግን ስርአቱ የተሳሳተ የሚጥለው አካሄያድ ነበር፤ ነውም፡፡ ይህ የረጅም ግዜ የዋህ ትግሌ ግን ኢሕአዴግን አይኑን እንዲከፍት ሊያደርገው አልቻለም፡፡ ምክናያቱም እነሱ ትኩረታቸው እራሳቸው ብቻ ይጠቅመናል ያላችሁት ሰው ላይ እንጂ፤ ቁምነገሩ ላይ ባለመሆኑ አፋችን እንድንሸብብ ያደረጋችሁን ሰዎች እንደነበርን የአደባባይ ሚስጥር አይደለም፡፡ ይቃወማል ብላችሁ የምትጠረጥሩትን ሰው፤ አይምሮውን የሚፈታተን፣ ስብእናውን የሚገድል፣ ስነልቦናውን የሚሙዋጥጥ፣ ማንነቱን እንዲያጣ፣ ታማኒነት እንዳያገኝ ማድረግ እና የገቢ ምንጩን በመምታት ለዲሞክራሲ እንዳይቆም በማድረግ ከጨዋታ ውጭ እንዲሆን ማድረጋችሁን አዙሮ ማየት መልካም ነው፡፡ ዲሞክራሲን እንፈልገዋለን ማለት ተቀናቃኝን በመምታት አልነበረም፡፡ ምንአልባት ተቃዋሚ ሆኘ ብገኝ እንኩዋን፡፡ ግን እንደእውነቱ ተቃዋሚያችሁ አልነበርኩም፡፡ ያቃታችሁ ግን እኔን ደጋፊ ማድረግ ብቻ ነበር፡፡ ይህንንም ያልቻላችሁበት ምክናያት የዲሞክራሲ ብቃታችሁ እና ፍላጎታችሁ ፈተና ላይ የወደቀ፤ የምትፈልጉትን የማታውቁ በመሆናችሁ ነው፡፡ እኔ ኢሕአዴግ ልሆን አልችልም፡፡ ምክናያቱም ከህዝብ ማሃል ህዝብ መርጦ የሚኖር ድርጅት በመሆኑ ነው፡፡ አውቃለሁ፤ ኢሕአዴግ ቢያጠፋም   አይቀጣም፤ ከእለት ወደእለትም ኢኮኖሚው ያድጋል፡፡ ችግር ቢደርስበት የእኛ ነው ተብሎ ጸጥታው በቶሎ ይረዳዋል፡፡ ስለዚህ በኢንቬስትሜንትም ውስጥ ሰው ልግባ ካለ፤ ኢሕአዴግ አባል ወይም አይን ያወጣ ደጋፊ መሆን አለበት፡፡ እንግዲህ ፋክቱን እንጋፈጥ ካላችሁ፡፡ ግን ደግሞ ተቃዋሚ ይሆናል እና ንግግሩ ህዝብን ያነቃቃብናል የምትሉትን ሰው፤  የወንጀል ድርጊት ሲፈጸምበት ጸጥታ አስከባሪ ሊያገኝ ቀርቶ፤ ጭራሽ ጸጥታውም አብሮ ተባባሪ ሆኖ ያሸዋል፡፡ እንግዲህ በጠራራ ጸሀይ ወንጀል ሲፈጸምበት እጅ በእጅ እየታዬ እርዳታ ቢጠየቅም የቁራ መጮሕ ይሆናል፡፡ ይህ አይምሮን የምታዛቡበት መንገድ ምን ያህል እንደሚጎዳችሁ እንኩዋን መገንዘብ አልቻላችሁም፡፡ እኝም እንዲህ አላደረግንም ብትሉም፤ የሚከወንበትን ፍጡር ግን የውሻችሁን ያህል አልቆጠራችሁትም፡፡

 በእውነት አይምሮ የእግዚአብሄር እንጂ የሰው ስላልሆነ፤ ሀሳብስ ከየት ይፈልቃል፤ ብላችሁ እንኩዋን እግዚአብሄርን ማስታወስ አልቻላችሁም፡፡ ሳኦል፤ አምባገነንነቱ አይሎ እግዚአብሄር የሰጠውን እረዳት ዳዊትን እንኩዋን ያሳድደው ነበር፡፡  ኢሕአዴግ አስተዳደሩን የሚቃወመውን ህዝብ፤ ወኪል እንዲያጣ ለማድረግ የሚያደርገው ጥረት እጅግ አሳፋሪ እና፤ በልማትም ልንረዳችው ያልነውን ሁሉ ያሸማቀቀ መሆኑን እንድትመለከቱት ያሻል፡፡ ጀመርነው ወይም እኛ ነን አስተማሪው የምትሉለትን ዲሞክራሲን የዝናብ ጸሀይ አድርጋችሁ፤ ብልጭ ድርግም ስታደርጉት መቆየታችሁ አልክደውም፡፡ ዲሞክራሲ አለ ብዬ እዛው ኢትዮጲያ ነበርኩእና አካሄዱን ሁሉ አይቸዋለሁ፡፡  ዛሬ ደግሞ፤ ወሰን ተሻግራችሁ እሰው አገር ሰው ጋር አብራችሁ አድማችሁ በትውልድ ኢትዮጲያዊ፤ በዜግነት እንግሊዛዊ የሆነውን ሰው አፍናችሁ እስር ቤት ከታችሁታል፡፡ የት እንዳለእና ደግሞም ያም የወሰናችሁበት ግድያ ይፈጸም እንደሆነም ሰብአዊነት ያለው ኢትዮጲያዊም የሆነ ወይም የሰብአዊ መብት ተሙዋጋች እና ስብእና ያተላበሰው ደጋፊዎቻቸው፤ አፍጥጠው በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ፡፡  አንድ ነገር ልበል፡፡

ምንም እንኩዋን አገርቤትም መመላለሱ፤ ልማት ሳይሆን፤ ልማት የሚደግፈው መንግስት እራሱ ኢሕአዴግ በጥርጣሬ እያዬ ህይወትን ከንቱ ያደረገብን ሰዎች ብንኖርም፤ ሌላውም የኢሕአዴግ ተቃዋሚ ወይም ነገሩን እያየውም ግራ የገባው፤ አምባገነን መንግስትን ደግፋችሁ እየተባልን ብንሰደብም የልማቱ ተጋሪ ለመሆን ወደሁዋላ ያላልን እንደነበር ልታውቁት ይገባል፡፡  ዛሬ የደረስኩበት ደረጃ ግን ባለፈው ዲሞክራሲ አለ እያልኩ የተመላላስኩበት የኢህአዴግ መንግስት እንድሸማቀቅ እና እንዳፍር ከነአካቴው አድርጎኛል፡፡ ምክናያቱም፤ ህዝብ በትክክል ግብር እንዲያስገባ እና የቫት ስርአትንም ጥቅም ለኢትዮጲያ እድገት አስፈላጊ መሆኑንም እና እንዲተገብረው ተናግሬአለሁ እና፡፡ ዛሬ ግን ግብር የሚገባው ለአንድ ፓርቲ መፈንጫ እየሆነብኝ መጥቶአል፡፡ ለነገሩ ጠቀስ ባደርገው፤ ዲሞክራሲ አለ ካለ፤ ለተቃዋሚም መንቀሳቀሻ እኮ የግድም አስፈላጊ ነው፡፡እንግዲህ ኢሕአዴጎች ከነእንግሊዝ ጋር እራሱን አወዳድሮአል እና፡፡ ኢህአዴግ ግን፤ ለየትኛው ተቃዋሚ ክፍል ነው ከከፈልነው ግብር የምትሰጣቸው  ብዬ ብጠይቅ ደስ ባለኝ ነበር፡፡ የለም አሁን አሁን ሳስበው፤ ግብር የምንከፍለው ለአንድ ፓርቲ ብቻ መገልገያ ከሆነ፤ እውን የኢትዮጲያ ህዝብ አገር ገብተን የምንቀሳቀሰውን፤ ኢንቬስት የምናደርገውን፤ ዲሞክራሲ አለ ብለን እየተመላለስን እየመሰከርን ያለነውን፤ ቢጠላን ትክክል ነው ለማለት የምደርስበት ደረጃ ላይ ደርሻለሁ፡፡ ተቃዋሚ ሳልሆን፤  ዲሞክራሲን በመናገሬ  ሰብአዊ መብቴንም  የተነፈኩበት አጋጣሚ በኢትዮጲያ ውስጥ ተለማምጃለሁ፡፡ አዎ ዲሞክራሲ የለም፡፡ ተጀመረ ያልነው በዳዴ እንኩዋን ሲሄድ የነበረው፤ ከነአካቴው ተመቶ መሬት ላይ ተዘርሮ ሞቶአል፡፡  የፈለገ ነብይ ይመስክርለት፤ የፈለገ የውጭ አገር ለኢሕአዴግ ይመስክርለት፤ ግን አንድ የኢትዮጲያ ህዝብ የሚያውቀው ሀቅ ዛሬ ተፈጥሮአል፡፡ ኢትዮጲያውያኖች ከውጭም አገር እየታፈኑ እየተወሰዱ ነው፡፡ የሚታፈኑትም ለ23 አመት ያለማቁዋረጥ ኢትዮጲን የሚገዛው፤ በመሳሪያ ሀይል ደርግን ጥሎ ዙፋን የጨበጠውን ወያኔ ኢሕአዴግ የሚባለውን የፖለቲካ ፓርቲ የሚቃወሙት ናቸው፡፡ ስንት ናቸው ቢባል፤ ሁሉም ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ናቸው፡፡ እኛን ኢሕአዴግ አልነካንም የሚል ካለ አቤት ማለት ይችላል፡፡ እነዚህ ሰዎች   አለም እንዳወጀው አይነት ሽብርተኞች አይደሉም፡፡ ከሁሉም የኢትዮጲያ ዘር እየታፈኑ እንደሚመለሱ በገተቃዋሚዎች ሲነገር አላምንም ነበር፡፡ ኢህአዴግን እንዲጠላ የሚያደርግ የተቃዋሚ ወሬ መስለኝ ነበር፡፡ ዛሬ ግን ከተቃዋሚዎች የምሰማው፤ በምእራቡ አለምም መታወጅ የጀመረው፤ አንድ የበላይነትን የተቀናጀ ፖለቲካ ፓርቲ ተቃዋሚውን ለማፈን ሽብርተኛ የሚለውን ቃል ይጠቀማል የሚል ነው፡፡ ከአገሩ የተባረረውንም ስደተኛ በአለም እንዳይኖር ለማድረግ ይጥራል ተባለ፡፡  እንዳውም፤ የሞት ፍርድንም ሀሰት እና አዳፍኔ አድሎ በሚደረግበት ኢትዮጲያ እውን ላመድረግ የሚሩዋሩዋጥ ስልጣን የጠማው ማለት ጀመሩ፡፡ አቶ አንዳርጋቸው በሚባለው የነጻነት ታጋይ እያንዳንዳችንን ምን እያደረግን እንዳለን፤ ለውነትስ እየተሙዋገትን እንደሆነ አይናችንን ከፍተን እንድናይ ሀ ብሎ ምእራፍ ከፋች ሆኖአል፡፡ እስከዛሬ ተቃዋሚ ሲጮህ፤ ዲሞክራሲ አለ ብሎ፤ ከደርግ በሁዋላ ምንም ስለኢትዮጲያ ለመስማት ጆሮውን የዘጋው አለም ዛሬ ይኮረኩረው ጀመር፡፡ 
 እንግሊዝስ ይህንን የመን የሰራችውን ስራ ትደግፋለች? አትደግፍም፡፡ የመን እና ምእራቡ አለም እኮ የከረረ ቂም አላቸው፡፡ ያ ብቻ አይደለም ምንአልባት ለታይታ ሊመስል ይችላል፡፡ ዛሬ ብትወድ ነገ የሚነሳባት አቁዋም የለሽዋ የመን፤ ውሎ አድሮ ተጠያቂነቱዋ አይቀርም፡፡ ምእራቡ አለም ቸኩሉ የሚሰራ አይደለም፡፡ ለአንዳልካቸውም ብቻ ሳይሆን ለሚጠይቁዋቸው ዜጎቻቸው፤ ለሰብአዊ መብት ሲሉ፡፡ ሰብአዊ መብት እኮ ብዙ ሚሊዮን ደጋፊ ህዝብ ያለው ድርጅት ነው፡፡ትክክል እንዲሰራ ደጋፊው ግፊት ያደርጋል፡፡ ደግሞ ሰብአዊ መብት ፖለቲከኞችንም ምርጫ ላይ ፈተና እንዲመጣባቸው ያደርጋል፡፡ ለምን ቢባል እሱ የሚጽፈው ሪፖርት በመራጩ ሕዝብ ይነበባል እና፡፡ ስለዚህ የእንግሊዝ መንግስት የሰበአዊ መብትን ጥሰት ይቃወማል፡፡ ምንአልባት ቸኩሎ እርምጃ ባይወስድም፤ ለኢሕአዴግ ግን አንድ ቀን ለፍርድ እሱን ለማቅረብ አንዱእና ትልቁ ነጥብ ይሆንበታል፡፡ ደግሞም የእንግሊዝ አገር በኢትዮጲያ ለምታደርገው የማንኛውም ልማት እንቅስቃሴ የሰብአዊ እርዳታ ከህዝብ ለማግኘት ፈታኝ ይሆንባታል፡፡ ምክናያቱም የምእራቡ አለም የሚያደርገው በአፍሪካ እርዳታ በህዝቡ ድሮም ጥያቄ አለው፡፡ ትክክል ሰው ያገኘዋል? እርዳታስ የሚሰጠው አገር ሕዝብ አስተዳደሩ በአምባገነን የተያዘ ነው? ብር ወደውጭ አውጥተው የሚያስቀምጡ መሪዎችን አትተባበሩም ሌላው ድብቅ ወቀሳ ነው፡፡ የዛሬው ሃይጃክ ግን ለሁሉም ጥያቄ አውንታዊ ነገር ሊፈጥር የችላል፡፡  እኔ ምንም እንኩዋን የተቃዋሚ ፓርቲ አባል ባልሆንም፤ ግን ተቃዋሚ መገኘት መንቀሳቀስ ያለበት አንድ የፖለቲካ ፓርቲ ስለወደደ ሳይሆን ግድ ስለሆነ ነው፡፡  ግልጽ ላድርገው፤  ያለውን መንግስት የአስተዳደር ብሉሽነት የሚቃወመው የሕዝብ ክፍል ተቃዋሚን ይፈልጋል፡፡ ተቃዋሚው በብልሹ አስተዳደደር ለተንገላታው፤ ለሚሰደደው፤ በሙስና፣ በበላይነት፣ በማንአለብኝነት፤ በሀሰተኛ ፍርድ፤ በኑሮው ውድነት የተንገላታ ህዝብም የሚፈልገውም አካል ነው፡፡ የደላውም ምንአልባት የሞቀው ጎጆው ሰብአዊነትን ካዘናጋው እና ለግፍ ጆሮውን ከደፈነ፡፡ በቃ ይህ ስለሆነ ተቃዋሚ ፓርቲ መታሰር መሰደድ መገደልም የለባቸውም፡፡ ዲሞክራሲእና መብትን አካሄዱን እንወቅ እንረዳ ካልን እነሆኝ ኢሕአዴግ ብያለሁ፡፡ በቸር ኑ የምላችሁ፤ አንዲት በሰብአዊነት ላይ ያገባኛል የምል  ባዩሽ አበበ ነኝ፡፡

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen