Samstag, 26. April 2014

እድገት የማያሳይ ፖለቲካ



እድገት የማያሳይ ፖለቲካ


ፈሪሃ እግዚብሄር በኢትዮጲያ ላይ እንዲኖር የፈለኩት ሀይማኖትን ለመስበክ ሳይሆን፣ ሰው እንደሰደድ እሳት በእራስወዳድነት የተጠመደበትን እና እኔ ብቻ ልኑር ልዳን የሚለውን አመለካከት እንዲመለከት በማስታወስ ነው፡፤ ይህም ለዚህ ያበቃኝ በቂ ሰዎች የደረሰብኝን ችግር እና ብዙዎች ደግሞ በመመልከት ከቶም በማሾፍ እና በመሳቅ እየተመለከቱ ማለፋችው እጅግ በጣም ገርሞኝ ነው፡፡ እንደኢትዮጲዊነት ደግሞ ይህ አሳፋሪ ምግባር ነው፡፡  እኔ በኢኮኖሚ እራሴን የቻልኩ ሰው ስለሆንኩ፤ እንደሰው ለመስራት እና ለማደግ የኢትዮጲያ ሁኔታ አልፈቀደልኝም እንጂ፤ እራብ ላይ ልወድቅ የማልችልበት እምነት እና ደግሞም ኢኮኖሚ ላይ ለመድረስ  ችያለሁ፡፡ ይህን ስናገር እርቦኝ ጥግ ይዠ ቆሜ የማለቅስ ሴት አልሆንኩም፡፡ ግን ሁኔታዎችን የግድ ለመጥቀስ እራሴን በኢትዮጲያ ያስቸገረኝን የብዙ  የሴት ችግር ስለሆነ በጋራ እንዲታወቅ  ልገልጸው እገደዳለሁ፡፡ እንጂ እንደሌባ ተኮፍሼ ትእቢተኛ መሆን አልፈልግም፡፡ በነገራችን ላይ ትክክለኛ ግብር ከፋይ ሆኜ አይኑ ለታወረው ኢሕአዴግ ጠቅሜዋለሁ፡፡ በወሬ ልጠቅመው ግን አልችልም፡፡ ተግባሬ መስራት እና እራሴን መቻል ነው፡፡ ይህንም አድርጌአለሁ፡፡ ከእሱ ግን ያገኘሁት አምስት ሳንቲም የለም፡፡ ሳንቲምን የምገልጸው በሚደረግልኝ ድጋፍ  ነው እንጂ እኔ ከኢሕአዴግ ቀርቶ ከሌላም በፖለቲካ ስም ፍጆታ አልፈልግም፡፡ ፍጆታዬ ህግ የበላይነት አለበት አገር ለመኖር መጣር ነው፡፡ ለሴት ይህ በጣም ጠቃሚ ነውእና፡፡ ገንዘቡ የሕዝብ ስለሆነ አልመኝም፡፡ በቃ ኢሕአዴግ ለእኔ ለሴቱዋ ያደረገው መከላከል  ዜሮ ነው፡፡ ምንም የረዳኝ ነገር የለም፡ያለው መንግስት ጣፋቱን እራሱ ማወቅ አለበት፡፡ እኔ ግን ችግሬ የፖለቲካ ፍጆታ ብቻ ሆኖ እኔ ሳልኖር እንዳልሞት ስለማልፈልግ እራሴ ችግሮችን ይፋ ለማድረግ ተገድጃለሁ፡፡ ሕግን ሳይሆን ሕግ አስከባሪውን እየፈራን የምንኖርባት አገር፡፡  ኢትዮጲያን ስመለከታት የአንድ ጉረኛ ሰው ቤት ትመስለኛለች፡፡ እሱም ሳሎኑን አሳምሮ ጉዋዳው የቆሸሸን፤ አልያም የአንዲት ሴት ወይዘሮ ሙያ፤ ጉዳጉዱ በተጥለቀለቀ ቅቤ የተሸፈነ፡፡
  „ብቻ የቄሰራን ለቄሳር“ ሀቄን የተወጣሁ ሴት ነኝ እና በእዚህ እኮራለሁ፡፡ ኢሕአዴግ ደግፎ ካሳደጋቸው ሰዎች እጅግ በጣም የተለየ ያልተስገበገበ  ማንነት ያለኝ ንቃተህሊና ያለኝ ሴት ነኝ፡፡ ስለዚህ በኢህአዴግ መንግስት እሱ ለእኔ ያልተወጣውን ግዴታ እንድወጣ እግዚአብሄር ቆራጥነቱን ሰጥቶኛል፡፡ ግን ለአንድም ችግር ደርሶልኝ የሚያውቅ ድርጅት አይደለም፡፡ አገራችንን የጣላት የአስተሳሰባችንን እድገት ቆልፎ ያያዘው የውስጣችንን ባዶነት በአፍ ለመሙላት የምናደርገው ጥረት ነው፡፡  በእርግጥ እኔ በሰው ላይ የማላደርገው ጨካኝ ተግባሮች በኢትዮጲያ ውስጥ ሲፈጸሙ አይቻለሁ፡፡ ይህም ከቀን ወደቀን እያደገ የሚሄድ እንጂ የሚቀንስ አይደለም፡፡ እንግዲሕ በኢትዮጲያ የፖለቲካ ማንአለበኝነት የሰፈነበት ቦታ ሕብረተሰቡን ፈር  የሚያሲዝ ሕግ መተግበር ካልቻለ፤ ያለን አማራጭ ህብረተሰቡ እግዚአብሄር የሚለውን ትክክለኛ መንገድ እርስበእርሳችን ተማምረን አገሪቱን መራራ እንባ በበደል የተነሳ እንዳይፈስባት ለመታደግ ያለን አማራጭ ወደእግዚአብሄር መመለስ ብቻ ነው፡፡ እንደእውነቱ ዛሬ ከጥጋብ በላይ የሳቀ ነገ ያለቅሳል፤ ዛሬ ያለቀሰ ነገ ይስቃል፡፡ ይሕ የማይቀር ሀቅ ነው፡፡ ይህም የምላችሁ፤ ሁሉም በፖለቲካ እያሳበበ መረን የለቀቀ ማንአለብኝነትን የሚያሳዩ ግለሰቦች ብዙወን ሰው መራራ ሕይወት እያስኖሩት እና የደም እንባ እያስለቀሱት ይገኛሉ፡፡ ባይመችም አንድ ነገር ለማለት እሞክራለሁ፡፡ ባይመችም የትግሌ ዋንኛው መሰረት ከጨቆነኝ እና ካሳደደኝ ማንአለብኝ የሆነ በትእቢት የተሞሉ ሰዎችን ባሕሪያቸውን መቃወም ነው፡፡ ምክናያቱም እኔም የመኖር መብት አለኝ እና ነው፡፡ ተዝናንተህ ሳሆን ተሸማቀህ የምታሳልፍባት ኢትዮጲያ ባንዲራ ብቻ እጃችን ላይ ጠምትመን ወይም እጆሮአችን ላይ አንጠልጥለን በመሄድ ለውጥ ልናመጣላት አንችልም፡፡
 እርግጥ ነው፤ ጡንቻቸው የፈረጠመ እና ብልሹ አመራሮችን መከታ ያደረገ  ወይም ያደረገች ግለሰብ ሊሆኑ ይችላሉ የሚያሳድዱ፤ ግን ይህ ብልሹ አመራር እስከሚጠፋ፤ እንዳው እንኩዋን እስከሚቀንስ መታገል ግድ ይለናል፡፤ በተለይ ሴቶች፡፡ ሴቶች ትዳርን ለፍቅር እንጂ ለኢኮኖሚ ደግሞም ባልን ለአብሮነት ለቤተሰብ እንጂ  ለመከላከል /ቦዲ ጋርድ/ ለማድረግ ለማይፈልጉ ለውጥን መመኘት አለባቸው፡፡ ካልሆነ ለመኖር እራሱ ሴት በኢኮኖሚ እራሱዋን ቻለችም አልቻለችም የብልሹ አመራሮች ተጠቂ ሆና ህይወቱዋ ውስብስብ ያለ እና ትዳሩዋም የፍቅር ሳይሆን እራሱዋን ለማዳን የቦዲ ጋርድ ቅጥረኛ ለመቅጠር እንዳይሆንባት ያሰጋል፡፡ ሁሉም ገቢውን ለማግኘት የመጣር እና እራሱንም የማስተዳደር ግዴታ ቢኖርበትም፤ ሌላው ደግሞ የሌላውን ሕይወት በመበጥበት ንብረቱን በመዝረፍ መሸጋገሪያ ድልድይ መሆን የለበትም፡፡ ኢትዮጲያ ግን የደቡብ አፍሪካ አይነት ሁኔታ በህብረተሰቡ መካከል እየታየበት የሚሄድ ሆኖአል፡፡ ለጊዜው ገዢው ፓርቲን ጥፋተኛ እያስደረገ የሄደው ስድነት የእያንዳንዳችንን በተለይ በኢኮኖሚ እራሳችንን ለመቻል ጥረት የምናደርግ ሴቶችን እያንገላታ እያሳደደ ወይም ደግሞ እዛው ለአላስፈላጊ ወጪ እንደጉቦ እና ደግሞ ላልፈለግነው ትዳር ወይም ተደራቢ ውሽማ ቢጤ እንድንይዝ የሚያስገድደን ስውር ሲስትም ውስጥ እንድንገባ እየተገደድን ነው፡፡ ይህን ለገዢው ፓርቲ ለማሳወቅ የጣርን አንዳንድ ሴቶች እንደፖለቲካ ተቃዋሚ እየታየን ተገለን ንብረታችንን እንኩዋን እንዳንሰበስብ ተደርገናል፡፡ ደግሞም ዲያስፖራ  ብለው በስም የተከፈለው ኢትዮጲያዊ በተለይ ሴቱ ለዘረፋ በእጅጉ የተጋለጠ ሆኖአል፡፡ ኑ ተራግፋችሁ ሄዱ ኤነት ነገር፡፡ ይህ ገዢው ፓርቲ ሊያፍርበት የሚገባው ነገር ቢኖር፤ በኢኮኖሚ እራሱዋን እንድትችል የምትጥርን ሴት ሊያበረታታ ቀርቶ እንደለለችም በመቁጥር ቀንዱዋን እያሉ የሚያስባርሩዋትን  ስውር ሌቦች ወይም ስውር የገባያ ተወዳዳሪዎች አሳልፎ ሰጥቶዋት ይገኛል፡፡ ነውርእና አሳፋሪ የሆነው ይህ ነገር ግን መቆሚያ ሊኖረው ቀርቶ እየባሰ እየሄደ ነው፡፡ ብዙዎቹ ገዢው ፓርቲ ቂጣቸውን ወደላይ እየገፋ  ያወጣቸው ግለሰቦች በዚህ መልኩ በደካማው ገንዘብ እና በሴቶች ገንዘብ ያደጉ ናቸው፡፡ ብቻ እኔን ብቻ አይቃወመኝ እንጂ እሱ ወይም እሱዋ በፈለገው መንገድ ይደጉ ማለት፤ ግብር ከፋዩን ህብረተሰብ በጣም ያስመረረው እና የሴቶችንም የኢኮኖሚ ትግል በእጅግ እየቀጨው እንዳለ እያየነው ነው፡፡ ይህ መቼ እንደሚሻሻል ባናውቀውም ግን ተጠቂዎች የምናነባው እንባ ለምድሪቱ በረከት የሚዘጋ እና የሰውንም የአይምሮ እድገት ተቆጣጥሮ የሚዘጋ ነው፡፡ ይህ ጋጥወጥነት እየሰፋ ከሄደእና ምንም አይነት ቆጥጥር የማይደረግበት ሁኔታ ፤ማንም ሰው ሊረዳው የሚችለው ቀምተው አስፈራርተው እና ደግሞም አሳደው የሚበሉ እራሳቸውንም ወደላይ የሚሳያሳድጉ ወንበዴዎች ቁጥር በሰፊው እያደገ የሚሄድ መሆኑን ከወዲሁ ማንም መረዳት ያለበት ሀቅ ነው፡፡ ሌላው ይህን ጉዳይ ዝም ብሎ ከገዢው ፓርቲ ጋር ብቻ በማያያዝ ማለፍ በኢትዮጲያ ላይ ያለው የባሕሪ ለውጥን ወደ  ስግብግብነት እና ማንአለብኝነትን ይሁንታ እንደመስጠት መሆኑን አውቆ፤ ተቃዋሚም ቢሆን በዚህ አይነት መጥፎ የባህሪ ለውጥ፤ነገ ለእሱም ቢሆን እንደማይመች እና የፖለቲካ  ሥራ እንቅፋት መሆኑን አውቆ በማንኛውም ሀይማኖት የመረጋጋት እና ሌላውን የመረዳት የመርዳት ትብብር ህብረተሰቡ እንዲላበስ የሚያደርግ ትምህርት ቢሰጥ መከላከል የለባቸውም፡፡ ለጊዜው የፖለቲካ ለውጥ በማታይበት አገር እምነት እጅግ በጣም የሞራል አስተማሪ መሆኑን መረዳት አለባቸው፡፡  በኢኮኖሚ እራሳቸውን ለመቻል ጥረት የሚያደርጉ ሴቶች እና ብሎም ደካማ ሰዎች ህብረተሰቡ ጉልበት፤ መከታ እና አለኝታ እንዲሆናቸው እንዲጠብቃቸው ትምህርት መስጠት ግድ ሊለው ይገባል፡፡ የተለቀቀ ወፍን መልሶ ማጥመድ አስቸጋሪ ይሆናል እና፡፡
ካልሆነ ሀይማኖት አያስፈልግም የሚቀድመው ሌላ ነው የሚል፤ ላም አለኝ በሰማይ ወተቱዋንም አላይ ይሆናል፡፡ የህግ የበላይነት በማይታወቅበት እና ብልሹ አመራራ ባለበት አገር መሪር እንባ እየወረደ ባለበት ሁኔታ የሴቶችን ጉዳይ እንዳለ መዝጋት ማለት እጅግ ሁዋላ ቀርነትን የሚያሳይ ነው፡፡  ሌላው የኢትዮጲያ አኑዋኑዋር ትንንሽ ማህበረሰብ መስርቶ ከመኖር እንዲወጣ ማንም የረዳው የለም፡፡ ይህም የሚያሳየው ሕግ አለመኖሩን እና አለመታወቁን ሲሆን በትንንሽ ግሩፕ መወሰኑ የሚያመለክተው፤ አንድ በግሩፕ ዘረፋ ሌላው ደግሞ በግሩፕ ሆኖ እራሳን ማዳን መከላከል ነው፡፡ ስለዚህ የኢትዮጲያ ፖለቲካ እንደትናንትናው ዛሬም ነገም ገደል የገባ እድገት የማያሳይ ሲሆን ጉራና ትእቢታችንም ከአፍ ያላለፈ  መሆኑን ለመረዳት ችያለሁ፡፡ አዎ ጉራ ብቻ፡፡ ቢሆንም በቸር ኑ፤ ለክሪቲኩ መለቴ ነው፡፡
ባዩሽ

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen