Mittwoch, 23. April 2014

ታሪክ ባህል ሲሆን





ታሪክ ባህል ሲሆን

ኢትዮጲያ ከ17ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ከውጭ ጥላት በመከላከል ብቻ ኖራለች፡፡ ይህም ብዙውን የኢትዮጲያን እድገት እንደልማት አይነቱን በእጅጉ ሰባብሮት አልፎል፡፡ ኢትዮጲያ እንደአነሳሱዋ እንዳትጉዋዝ ያደረጋት ጊዜዋም መከላከል ስለወሰደባት ነው፡፡  ያው መከላከል ልምድ ሆኖብን ደግሞ በገሀድ የምናየው የውጭ ጥላትም ባይኖር፤ አሁንም ግን የፊውዳሉ ስርአት የሀይለስላሴ መንግስት እረጅም ግዜ የእራሱን ህዝብ ፖለቲካሌ የሚቃወመውን ቀንዱን እየሰበረ እረጅም ግዜ መቆየቱን አንክደውም፡፤ ጭራሽ ዙፋኑን እንኩዋን ንጉሱ ላልጋወራሹ ለማስተላለፍ በጭራሽ እምነት አልነበራቸውም፡፡ ይህ መረጃው ለማንም ቢሆን ግልጽ ነው፡፡ ሀይለስላሴ እድሜአቸውም ገፍቶ እነኩዋን ለወለዱት ልጅ ዙፋኑን ለማስተላለፍ አልደፈሩም፡፡ አላመኑም፡፡ መከላከል ዘይቤ ሆኖ ፤   እነመንግስቱ ነዋይ ለእኛ ግልጽ ባልሆነ መልኩ ወይም ታሪኩን እስከዛሬ ግልጽ ባልሆነ መልኩ በስቅላት ተቀተዋል፡፡ የእያሱም ጉዳይ አከራካሪ ሆኖ ብዙውን ያስኮረፈ እና ያስቆዘመ ነው፡፡ እኔ ሰሞኑን የንጉሱን ታሪክ የያዘውን ፎቶ እንኩዋን በግለጽ ባወጣ፤ ከየቦታው የሚወረወረው ተቃውሞ፣ ቀላል አልነበረም፡፡ ግን ንጉሱ ወደድንም ጠላንም ታሪካችን ሆነው አልፈዋል፡፡ ሌላው ደግሞ ትልቁ ቀውስ ደርግ ፊውዳሉን ገለሰሰኩ ብሎ እጅግ ብዙ ምሁሮች የሞት ሰለባ ማደርጉ ነው፡፡ ሁሉም በይፋ እና በአደባባይ ነው የገደሉት፡፡ ጭራሽ እንደአምልኮ ግንቦት ወር በኢትዮጲያ እጅግ የተፈራ እንደሆነ ልቦናችን ያውቀዋል፡፡ ልክ ደም እንደሚጠማ ወር ታይቶ በደም የሚዘክሩት ብዙዎች ናቸው፡፡ በግንቦት ደምን ለማድማት የሚሮጡ ብዙዎች ናቸው፡፡  ሲያደሙም እናያለን፡፡ በግንቦትም ወር ብዙ የመንግስት ለውጥ ይሆናል ብሎ የሚያምንም አይጠፋም፡፡ ይህ ግንቦት መጣ ብሎ የመንግስትን ለውጥ የሚመኝ አለ ደግሞ የሚፈራም አለ፡፡ እንግዲሕ ሚስጥሩን እግዚአብሄር ይግለጸው፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ደርግም የውጭ ጠላት ሳይመጣበት ልማት የለ ምን የለ ሲከላከል የነበረውን ተቃዋሚውን ነበር፡፡ ይህ የቅርብ ግዜ ምስክር ነው፡፡ እጅግ ብዙ ተቃዋሚ የከበበው ደርግ የቅርብ ግዜ ትዝታ ነው፡፡ ከዚያም ወያኔ ኢሕአዴግ ገብቶአል፡፡ እሱም ዛሬ የምናየው የውጭ ጠላት የለውም ግን የሚኖረው  ተቃዋሚውን በመከላከል ነው፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ ይፈራል ግን ዲሞክራሲ አለ ይላል፡፡ ፐሮፖጋንዳውም ሆነ ሁሉም እርምጃው እራሱን ትክክለኛ ተቃዋሚውን ደግሞ እንደጠላት አድርጎ አለምን በማሳመን ብዙ ድካም የሚያደርግ እና ብዙ ወጪ የሚያደርግ ፤ እንደሌሎቹ የእራሱን ዘሩን ከፋፍሎ ተቃዋሚ ብሎ በመከላከል የተቀመጠ መንግስት ነው፡፡ ለእኔ አዲስ ነገር የለም፡፡ አስራሰባተኛው ክፍለዘመን ያመጣብን ድኝገተኛ ጦስ ለምዶብን መሰለኝ በመከላከል እንኖራለን እንጂ የፖለቲካ ስራ የሚሰራ ገዢ አላገኘንም፡፡ ስለዚህ ቀኑን ባናውቀውም አንድ ቀን በድንገት ይህ መንግስት ይለወጣል፡፡ የተከላከሉ ሁሉ ከመውደቅ ድነው አያውቁም፡፡ ካየነው ልምድ፡፡ ስለዚህ ዘወትር አንዳንድ ሰዎች ተቃዋሚ ወይም ደጋፊ እንድንሆን ይመኛሉ፡፤ ደግሞም ፔንጤው ፔንጤ፤ ኦርቶዶክሱ ኦርቶዶክስ፡፡ ግን እባካችሁ መጀመሪያ እራሱን ያላወቀውን፤ ሌላውን እንዲሆን አትመኙ፡፡ እናንተን መሆን ሳስብ የሚከተለው መደነጋገር ነው፡፡ የእናንተን አላውቅም በመቃወም ወይም በመደገፍ አይደለም ነጥቡ ፤ ነጥቡ የምንቃወመውን ነገር ለይተን ማወቅ ነው፡፡ መቃወም መቃወም መንግስታቶቻችን ሁሉ በመቃወም አሳልፈዋል፡፡ ኮሎኒን ተቃውመዋል ደግሞም ዘራቸውንም አሁንም እየተቃወሙ በመከላከል እንደቆቅ ሆነው ጆሮአቸውን አይናቸውን አቁመው ይኖራሉ፡፡ ልምድ ያመጣው ካልሆነ ምን ሊሆን ይችላል፡፡ እንደምትወድቅ እያየህ ዘላለም በወጣደር እየተጠበክ መኖር፡፡ ለዚህ ጥሁፍ መነሻ ያደረገኝ ቃል በግል የመጣልኝ ስድብ መሰል ክርቲክ ነው፡፡
Looks like you are knowingly or unknowingly confused. ..cheating your self. ..and increasingly becoming a laughing stock. If you run out of ideas please take your time and come up with something relevant. ...otherwise you better keep your crap for your self.”
እየሳቁብሽ ነው አይነት ነገር፡፡ እርግጥ ነው፡፡ ለሚስቁ ማልቀስ ነው፡፡ እንጂ እንግዲህ አልናደድም፡፡ ምክናያቱም አረማመዴ መሬት የተረገጠ ካልሆነ እሰበራለሁ፡፡ አያችሁ ፔንጤው ፔንጤ፣ ኦርቶዶክሱ ኦርቶዶክ፣ ደግሞ ተቃዋሚው ተቃዋሚ፣ ገዢው ፓርቲም እሱን እንድትሆንለት ስለሚፈልግ ይናደዳል፡፡ ግን ሁሉም የእራሱን ባህሪ አይመረምርም፡፡ ማንንም እንዳንሆን ፊት ለፊቴ ቆሞ የሚናገረው ንግግር ያግደኛል እና፡፡
ለማኝኛውም በመከላከል  ለዘመናት የኖረ ህዝብ የማጥቃት ልምምድ አለማድረጉ ችግር ላይ ጥሎታል፡፡ በዚህም የተነሳ ኢሕአዴግ ሰላማዊ ሰልፍን ይፈቅዳል ብዬ አልገምትም፡፡  ምክናያቱም ይህ ባህሪ የፖለቲካችን ባሕል ሆኖአል እና፡፡ ብዙ ወዳጅ የለለው፤ ያደፍጣል፡፡ ብዙ ወዳጅ ያለው ደግሞ ውጣ ውጣ ይለዋል እና፡፡ እባካችሁ ተቃዋሚ ነሽ ደጋፊ አትበሉኝ፡፡  መደነጋገርም ካላችሁት ባህሬየን ያልተደናገረው አንድ ሰው ስሙን ጥሩልኝ፡፡ ያልኩት አድርባዩን አይደለም፡፡ ይህ በሁሉም አለእና፡፡ ስሙን ደብቆ እንደለቡ የሆነውን፤ እኔ ስሜን እና ፎቶዬን ያወጣሁትን እሱ ተደብቆ የሚለውን እንድልልት ሲፈልግ ከት ብዬ እስቃለሁ፡፡ ይህ ለዘመናት ያለፍንበት ነው፡፡ ኢትዮጲያ ከመከላከል አስተሳሰብ ካልወጣች በመሸነፍ እና በማሸነፍ፤ በጀግና እና በፈሪ ባህል ለሚመጣውም ዘምን እንኖራለን፡፡ ታሪክ ባህል ሲሆን  እንዲህ ይመስላል፡፡ በቸር ልበላችሁ፡፡
 
ባዩሽ

Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen