Sonntag, 31. August 2014

የሕይወት ልምድ በጨለፍታ



የሕይወት ልምድ በጨለፍታ


 እና ታላቅ የፈጣሪ ችሎታ ምስክርነት  


የሚገርመው አንድ ግዜ ሆስፒታል ገብቼ ነበር፡፡ እሱም ካንሰር አለብሽ ተብዬ ነው፡፡ ለእኔም ይህ ሁኔታ በጣም አስደንጋጭ እና አሳዛኝ ነበር፡፡ ጭራሽ የሚገርመው ከጎኔ ማንም የሚያጽናናኝም አልነበረም፡፡ አንድም ሰው፡፡ አዎ ከሰው ተፈጥሬአለሁ፤ ግን ምክናያቱን በማላቀው ነገር ከኢትዮጲውያን ወገኖች ያልታደልኩ ሆኛለሁ፡፡ ውነት እግዚአብሄር ይህን አውቆ ይሆን ባልበሰለ እድሜዬ ጀምሮ ለፈረንጅ አገር ያበቃኝ፡፡ ፈረንጅ አገር ዘመድ የለለውንም የሚያስታምም፤ የሚያበላ የሚያጠጣ፡፡ በዚህ የተነሳ ነው አንድ አገር ላይ ጥሩ ሲስተም ያስፈልጋል ብዬ የህግን የበላይነት እንዲሰፍን የምናገረው፤ የምተቸው፡፡ ካንሰር አለብሽ የሚለው ነገር በእጅጉ አስደንግጦኝ ስለነበር፤ ያልደወልኩበት ዘመድ አዝማድ ጎረቤት የአገር ሰው የለም፡፡ ወይም የማውቀውን ሰው ሁሉ ደውያለሁ፤ ግን አንድ ሰው ብቅ ብሎ ያጽናናኝ የለም፡፡ የሚገርመው እነሱ ጉንፋንም ሲይዛቸው ዘመድ አዝማድ ያጅባቸዋል፡፡ አይቻለሁ በእህቶቼ በወንድሞቼ፡፡ እነሱ ግን አለሁበት ቦታም ቢገኙ ብቅ ብለው ሊጠይቁኝ አልፈለጉም፡፡ ሌላ ቀርቶ በስልክ እንኩዋን የሚጽናናኝ አላገኘሁም፡፡ እኔ ግን ድንጉጥ ነኝ አልቃሻ ነኝ፡፡ እንዳውም ዛሬ ዛሬ ሳስበው፤ ሰውን እንዳፈቀርኩት የፍቅር ምላሽ ባገኝ ኖሮ፤ በእግዚአብሄር ሳይሆን ዘመድ ወገን ጉዋደኛ አምላኪ ሆኘ እቀር ነበር፡፡ ባጠቃላይ ብቸኛ ነበርኩ፡፡ ወልጄ መታረስ የሚባል አላውቅም፡፡ ሰው ጭክን ያለብኝ ሴት ነኝ፡፡
ይገርማል ከቶ ለዚህ ይሆን ወደዚሕ ወደተረጋጋ ሲስተም፤ ዘመድ አዝማድ አብላኝ አጠጣኝ የማትልበት አገር ከልጅነቴ ጀምሮ ከወሎ አውጥቶ አዲስ አበባን አቁዋርጦ እዚህ ቁጭ ያደረገኝ፡፡ እውነት ነው፤ አስቀድሞ የሚጨነቅልህ ጌታ ብቻ ነው፡፡ የወደፊቱን የሚገጥምህን እሱ ያውቃል እና ያዘጋጃል፡፡ ግና ከበሽታው ይልቅ ጠንከር ያለብኝ ዘመዶቼ ምንእንደሚያስቡ እና የዘመድ ሀቅ ባለመወጣታቸው አዘንኩ፡፡  በጣም የፈለኩዋቸው ወቅት ነበር፡፡ ነፍስ እንኩዋን የተጋደለ ይቅር ይባባላል፡፡  ያለፈው 23 አመታት ሙሉ የሰው ትም የጠማን ብቸኛ ነበርኩ፡፡  እነሱ ተሰባስበው የሚደርጉት ነገር ሁሉ ላይ ተጋብዠም አላውቅ፡፡ ሰርግ እንኩዋን ደግሰው የሚነጥሉኝ ትዝ ሲለኝ እረበሻለሁ፡፡ ግን ጌታ እኔ እያለሁ ይላል፤ ሁሉነገሬን ማቃለል ዘዴ የሚዘይድልኝ አምላኬ፤ አይምሮዬን ባይቆጣጠር ኖሮ የምሆነው ትዝ ሲለኝ ከክርስቶስ ጋር ያለኝ ፍቅር ጭራሽ ጥብቅ ክርር እንዲል ያደርገዋል፡፡ ክርስቶስ አዎ ፍቅር ነው፡፡ ወድ ወዳጆቼ ይህን የምጽፍላችሁ የግድ ስለአምላኬ መመስከር ስላለብኝ ነው፡፡ ክርስቶስ  ያልተወኝ ያልጣለኝ፡፡ ሳያንኩዋካ የሚገባው፡፡ የሚያጽናናው፡፡
የካንሰሩ ጉዳይ ቀኑ ደርሶ ወደ ኦፕሬሽን ልገባ ስል፤ ደም ስለሌለሽ ቶሎ ወደ ክፍልሽ በቶሎ ላትመለሽ ትችያለሽ ብለው የሚረብሽም ነገር ጨመሩልኝ፡፡ አዎ ኮማ ውስጥ የሚያስገባ ሪስክ ላይ ነሽ በማለት በካንሰሩ ላ ጨመሩልኝ፡፡ የመጨረሻውን ልጄን ወልጄ ገና ሶስት ወሬ ነበር፡፡ በደስታ የወለድኩትን ልጅ በሁለታችን መካካል ልዩነት ሊያመጣ ሰይጣን በሰፊው ሊገዳደረኝ እንደተነሳ አወኩት፡፡ ሁለት ለየት ያሉ ህልም መሰል እራእዮች ግን አይቼ ነበር፡፡ ስለእግዚአብሄር እምነት እንጂ አካሄዱን የማላውቀው ግን እስከዚህም እራእዮቹን ማጤን አላሰብኩም፡፡ ተውኩት እረሳሁት፡፡ ብዙ ህልም የማላየው ግን መልሶ መላልሶ ወደህልሙ እሳባለሁ፡፡ ግን ነገሮች ሁሉ ልክ እንደህልሙ መቀጠል ጀመረ፡፡ መጀመሪያ ምንም ደም ሳያስፈልገኝ፤ ሀኪሞቹም እንዳሰቡት ሳይሆን ኦፕሬሽኔን ጨርሼ ወዲያው ቆም አልኩ፡፡ ይገርማል ኦፕራሹኑም አላመመኝም መድሀኒት ማደንዘዣም አላስፈልገኝም፡፡ እኔ ግን ስለህልሙም ስለእግዚአብሄርም አላስብም ነበር፡፡ የማስበው፤ የሚጎበኘኝ ሰው ይመጣል፤ አበባ ይዘው ቸኮላቱን ምናምኑን ይዘው፤ ብሶቴን ሊካፈሉ ቁስሌን ሊጠይቁኝ፡፡ ግን የጠበኩዋቸው የውሃ ሽታ በመሆናቸው አዘንኩ፡፡ ከቁስሉ ይልቅ ህመም የሆነኝ ሰው አልባነቴ ነበር፡፡
የተኛሁበት ሆስፒታል ጀርመን ውስጥ በጣም ትልቁ እና ምርጡ ነበር፡፡ ያለሁትም ካንሰር የታመሙ ጀርመኖች መካከል ነው፡፡ በአሰቃቂ ሁኔታ ያሉ መካካል ተኛሁ፡፡ መጽሃፍ ቅዱስ ብቻ አጠገቤ አለ፡፡ በዛን ሰአት ስድስት አመቱ የነበረው ልጄ አጠገቤ መጥቶ ጋደም አለ፡፡ „ማማ አይዞሽ ስትሞቼ አበባ ሁልግዜ መቃብርሽ ላይ ይዠልሽ እመጣለሁ አልልይሽም፡፡ ትናፍቂኛለሽ እና፡፡ ግን ማማ አንዳንደዬ ከመቃብሩ መውጣት አትችይም፡፡ ለመቻል ግን ሞክሪ“  አለኝ፡፡ አዎ ትሞታለች የሚል እንጂ አይዞአችሁ ድና ትመጣለች ብሎ ያጽናናቸው ወዳጅ እንዳላገኙ ተረዳሁ፡፡ ሰይጣን የሚያውጀው በእኔ እና በልጆቼ ላይ ፍርሀትን መለየትን የመሳሰለ ነገር ነው፡፡ ደግሞም የተኛሁበት ሆስፒታል ልጆቼ ካሉበት እራቅ ያለ ስለነበር የማያቸው በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ነው፡፡ አልጋ ላይ ጋደም እንዳልኩ ዘወትር አንዲት መስቀል በመስኮቱ እራቅ ብላ ትታየኛለች፤ እኔም እሱዋን እያየሁ አነባዬን አፈስ ነበር፡፡  ያቺ በእሩቅ ለች ቤተክርስቲያን ጫፍ ላይ ያለች መስቀል እግዚአብሄርን ዘወትር እንዳስበው አደረገችኝ፡፡  አጠገቤ የተኛችው ሁለቱን ጡቱዋን የተቆረጠችው አንዲት ምሁር ሴት አልፎ አልፎ ታጫውተኛለች፡፡ „ ታድለሻል ፕሮፌሰሩ ሁላ የወድሻል“ በማለት የታዘበችውን ትነግረኛለች፡፡ አዎ በጣም ነው የሚንከባከቡኝ፡፡ እኔም ሳቅ ስለምወድ ፈገግታ ከፊቴ አይጠፋም፡፡ ካንሰር ግን ተስፋ አስቆርጦኛል፡፡ የልጆቼ ነገር አሳስቦኛል፡፡ ጥርሴ ይሳቅ እንጂ ውስጤ ግን ቀልጦአል፡፡ ሀኪሞች ምን ቢወዱኝ ካንሰርን ከሌላው የተለዬ  ፈውስ ታአምር መፍጠር አይችሉም፡፡ ሶስት ሳምንት ከተኛሁ በሁዋላ ግን፤ አንዲቱዋ ዶክተር ጠራችኝ፡፡ እኔ ስጠባበቅ የነበረው የትኛው ኦርጋኔ  ይወጣ ይሆን? መቸስ የኬሚካል ትርቲመንቱን እቀጥል ይሆን ብዬ ተጨናንቄአለሁ፡፡ የሚያረጋጋ ታብሌትም እንድወስድ ጠይቀውኛል፡፡ የተኛሁት ስንት ማሽን አፋቸው፣ አፍንጫቸው እና አካላቸው ላይ የተተከሉባቸውም አሉ፡፡ አንድ ክፍል ሁለት ብቻ ብንሆንም በአጠገባችን ያለው ሁሉ በአሰቃቂው ካንሰር የተለከፈ ነው፡፡ ህክምናውም አሰቃቂ እና ህመም ያለው ነው፡፡  እተጠራሁበት  እዶክተሮቹም  ቢሮ እንደገባሁ ፊት ለፊት ተቀመጥኩ፡፡ የምታነጋግረኝ ዶክተሩዋም እንዲሕ ስትል መናገር ጀመረች፡፡ „ እኛ በአንንቺ ውስጥ ታይቶአል  የነበረውን ካንሰር አጥተነዋል፡፡ በጣም የሚገርም ነው ብላ ሳትጨርስ ተወርውሬ አንገቱዋን ተጠመጠምኩባት፡፡ በጀርመን አገር ሰው ደስ ሲለው ዘሎ ማቀፍ ነው፡፡ እሱዋም እኛ ኦፕሬሽን በማድረጋችን አዝነናል በማለት በማዘን ተደናግጣለች፡፡ የእኔን መልስ የጠበቀችው እንደሚመስለኝ፤ ንዴት አልያም ወይ እከሳለሁ ምናምን እንድል መሰለኝ፡፡ እኔ ግን  በተለያዩ ሀኪሞች ጋር ሄጀ ካንሰሩ አለብሽ እንዳውም በጣም አግሬሲቭ ስለሆነ በአስቸኩዋይ ኦፕሬሽን አድርጊ ተብያሉ፡፡ እኔም ሀኪሙዋን፤ አትጨነቂ  አልኩዋትእና  ካንሰሩ ነበር ግን  እግዚአብሄር አስቀድሞ ፈውሰኛለው በማለት >ያየሁትን ህልም ልነግራት ጀመርኩ፡፡ በህልሜ አንድ ሰው ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፡፡ እሱም የወረደበት ቦታ ላይ ብዙ ህዝብ ተሰልፎ ይጠባበቀው ነበር፡፡ እኔም ከተሰለፉት ውስጥ ሶስተኛ ተራ ቁጥር ላይ ነበርኩ፡፡ እኛም ፈራጁእና ፈዋሹ ስለሚመጣ እሱ ጋር እንቀርባለን ብለን ነበር ወረፋ የያዝነው፡፡  ግን ይህን የምነግርሽን ህልም ያየሁት ሀኪሞች ካንሰር እንደተገኘብኝ ሳይነግሩኝ ቀድሞ ነው፡፡  ተራም ደርሶኝ ፈራጁ እና ፈዋሹ ጋር ቀርቤ ነበር፡፡ እኔ ገና ምንም ሳልናገር፤ „እዚህ ምን ታደርጊለሽ ፈውሸሻለሁ  ብየ ነግሬሽ የለምእን ?ለምን አታምኒም? ብሎኝ ነበር አልኩዋት፡፡ ግን የቀውስ ንግግር እንደሚመስል አውቃለሁ፡፡ እንኩዋን ለፈረንጅ  ያውም ሳይንስን በሚያምኑ ሀኪሞች እምነት አለን ለሚሉ ሰዎችም ይከብዳል፡፡ እናም ለእራሴ አልተቀበልኩትም ነበር እና ቅዠት መስሎኝ ነበር፡፡ ይህን ህልም ያየሁት ኦርቶዶክስ ውስጥ እያለሁ ነው፡፡  ለነገሩ እሱዋን ተሰናብቼ ከሆስፒታሉም እንድወጣ ተነግሮኝ ወደክፍሌ ሄድኩ፡፡
ክፍሌም ገብቼ ትንሽ ጸጥ በማለት አንድ ወቅት ያየሁትን  ህልም መሰል እራእይ ትዝ አለኝ፡፡ ያለምኩት ጀርመን ሆኘ ነው፡፡ ግን ህልሙ ተውኒቱ ኢትዮጲያ ነው፡፡ እንዲህ ልንገራችሁ፡፡ ብዙ የኢትዮጲያ ህዝብ የተሰበሰበበት አንድ አካባቢውን የማውቀው አንባ ላይ እኔም እዛ ተገኝቼ አየሁ፡፡ ግን እኔን አንድ በፍጥረቱ እንደእስስት የሚመስል አውሬ በጥርሱ የእጀን አንገት ነክሶ ይዞታል፡፡ እኔም እጅግ ተጨንቄ እጮሃለሁ፡፡ የሚያላቅቀኝ አጥቼ እራወጣለሁ፡፡ ድንገት ግን አንድ በፈረስ ላይ የተቀመጠ ሰው እየጋለበ ይመጣል፡፡ ሌሎች ፈረስ ጋላቢዎችም አጅበውታል፡፡ እሱም ወደእኔ በመገስገስ መጣእና „እጅሽን ወዝውዠው አይዞሽ ወዝውዥው“ በማለት እተለዬ ፈረስ ላይ የተቀመጠው ሰው በፈረሱ ዙሪያዬን ይዞረኝ ነበር፡፡  እኔም በሃይል ወዘወዝኩት፡፡ ያ አውሬም ተምዘግዝጎ በእርቀት ከእኔ ተለይቶ  ወደቀ፡፡ እጄን ግን በጥርሱ በስቶት ምልክት ትቶ ነበርእና፤ እንደገና ሰውየውን እየተከተልኩ ነክሶኛል መርዞኛል መርዞኛል ስል ተመልሶ እየጋለበ መጣናእና ከመቅጽበት እጁን እራሴ ላይ ጫን አድርጎ „ፈውሸሻለሁ“ በማለት እንደውሃ በሚፈስ ድምጽ „አይዞሽ አይዞሽ ተፈውሰሻል“ እያለ እንደመጣ ከመቅጽበት ከህዝቡ መሃል ወጥቶ ይሄዳል፡፡ ብንን ስል ግን የነከሰኝ አውሬ ከፊቴ ሊጠፋ አልቻለም፡፡ ወዳውም ለአንድ ቅርብ ሰው ህልሙን ነገርኩት፡፡ እሱም እና አትጨነቂ እባክሽ እኔ አንድ ግዜ አለም ጨልሞ አይቼ ነበር፡፡ ግን እስከአሁን አልጨለመም በማለት ሊያስቀኝ ቢሞክርም እኔ ግን ያ አውሬ ሳቄን ወስዶታል፡፡ የሆነ ፈተና እንደሚመጣብኝም ብረዳ ግን ፈውሸሻለሁ የሚለውን ለማመን እኔ ማነኝ ፈውስን አያለሁ በማለት እምነቴን እራሴን መመርመር ጀመርኩ፡፡  ህልሙ ህይወቴን ቀየረው፤ መጽሃፍ ቅዱስንም ማንበብ ጀመርኩ፡፡ ልጄን ወልጄ ኢትዮጲያ ይዠ ልሄድ ስነሳ አሞኝ ላደረኩት ምርመራ ካንሰር የሚል ምላሽ በስልክ ተደወለልኝ፡፡ በአስቸኩዋይ ወደኦፕሬሽን እንደሄድ ተወሰነ፡፡ አስቀድሞም ኢትዮጲያ ለመሄድ ፕላን ነበረኝ እና ኦፕሬሽን ሳልገባ ለመሄድ ወስኜ  ስለነበር ወደኢትዮጲያ ሄድኩ፡፡ ግን ደስታዬን ሁሉ ያ አውሬ ቀይሮታል፡፡ አውሬውም ካንሰር ሆኖአል፡፡ ኢትዮጲያም ደሴ እንደሄድኩ የሚካኤልን ባእል ለማክበር ወደደሴ ሚካኤል አመራሁ፤ ግን እዛ ከነበረበት ቦታ  ሚካኤል ተነስቶ ሌላ ቦታ እንደሆነእና እዛም ቤተክርስቲያኑን ለመስራት የመሰረት ድንጊያ ስለሚጣል በሙሉ ህዝቡ እዛ ነው አሉኝ፡፡ እኔም ወደዛ አመራሁ፡፡ ብዙ ህዝብ ተሰብስቦአል፤ የአመቱ ሚካኤል ነበር እና፡፡ አንድ ነገር ግን አስደነገጠኝ፤ እነዚህ ሰዎች ልክ አውሬውን ነክሶኝ እንዳየሁት ተሰባስበዋል፡፡ ጀርመን ሳለሁ ያየሁት ህልም አንባውም ቦታውም ይህ እራሱ ሆኖ አገኘሁት፡፡   በድንጋጤም ለየት ብዬ ቁጭ አልኩ፡፡ እግዚአብሄር አይሳሳትም፡፡ ሰው መቼም ሰው ሲመሰክርለት ለማመን ይሳነዋል፡፡ እኔም ብሆን በዛን ወቅት ሰው ቢመሰክርልኝ ለማመን እቸገራለሁ እና፡፡ ሳይንስ ቀዶ ስለሚያረጋግጥ እና መረጃ ስለሚያቀርብ እነሱ የሚሉትን ቶ እንቀበላለን፡፡  ግን እግዚአብሄር የሚያደርገው ማዳን ሳይቀድ ሳያደማ በመሆኑ ለማመን ይቸግራል፡፡ ከሆስፒታሉ ስወጣ ያቺ ሁለቱንም ጡትዋን የተቆረጠችው ምሁር ሴት፤ የምታነቢው ግን ምን ነበር አለችኝ፡፡ እኔም ባይብል ነው አልኩዋት፤ እኔ ግን አንብቤው አላውቅም በማለት አርቃ ወደዛች እኔ ስተኛ ወደማያት በሩቅ ያለች ቤተክርስቲያን  ተንጠራርታ አያየች በሃሳብ ሰመጠች፡፡ እኔም መልካሙን ተመኘሁላትእና ከሆስፒታሉም ሀኪሞቹን አመስግኚ ወጥቼ ሄድኩ፡፡ ይህ የሆነው ከአስራ ስምንት አመት በፊት ነው፡፡ እንኩዋን በካንሰር በጉንፋንም ወደሀኪም ቤት ሄጀ አላውቅም፡፡ በእርግጥ በኢትዮጲያ ውስጥ ያየሁት አንዳንድ ግፍእና መከራ ለስነልቦናዬ ፈታኝ ሆነውብኛል፡፡ መቼም ኢትዮጲያ አገሬ ናትእና ትናፍቀኛለች፡፡ የህግ የበላይነት የማያውቀው አኑዋኑዋራችን በጣም ያሳስበኛል ይረብሸኛል፡፡ ለእራስችንም ምን ያህል እውነተኞች እንሆን ብዬ እራሴን እጠይቃለሁ ፡፡ ሁልግዜ በፖለቲከኞች ላይ የምናሳብበው ነገር ይበዛል፡፡ ግን ፖለቲከኞች ደግሞ የእኛን አጋዥነት የሚጠይቁ ናቸው፡፡ እራስን ወዳድነት እና ማንአለብኝነት በህዝብ ማሃል የገባ ነው፡፡ ብዙ ጉዳቶች በውስጤ አሉ፡፡ የእኔን መሰል ደግሞ በሚሊየን ይኖራሉ፡፡ ብዙውን ነገር ግን አናወራውም፡፡ አንነጋገርበትም፡፡ የአስተሳሰብ ባህላችን የግልጽነት ሁኔታችን ለውጥ ካላመጣ፤ ጥሩ ሲስተምም መመስረት ቢቻል እውን ለማድረግ ብቃቱ ያጥረናል፡፡ የባህሪ ለውጥ የአይምሮ እድገትን ያመጣል፡፡ ባህሪችን ሲለወጥ የሌላው አዘን አዘናችን ይሆናል፡፡ ከዚህ የህይወት ልምድ ተነስቶ እንግዲህ ሰው እራሱን ይመርምር፡፡ ጌታ ከሁላችሁ ጋር ይሁን፡፡
ባዩሽ

Samstag, 30. August 2014

ዳንኪራ

ዳንኪራ
ታድልህ ይሆን ወይስ  ለመከራ
ባላደረከው ነገር ስምህ ሲጠራ
የለም የለም እኔ አይደለሁም፣
አላደረኩም
አልዋሸሁም አልቀጠፍኩም
ብለህ ብትናገር ብትለፈልፍ
ጠበቃ አብዝተህ ብታሰልፍ    
ዕድል ይሆን መከራ
ስምህ የሆነው መራራ
ዳኛው ሲገለምጥህ ሲያንገላታህ
መብት አለኝ፤ አለኝ ልናገር
ዳኛ ፍቀድልኝ ለእውነት ቆሜ ልከራከር
አንተም ፖሊስ ተወኝ አትጎትትኝ
ለግርብረት አታቻኩለኝ
ከእኔ ጋር እውነት አለች
በቀኑዋ ትፈርዳለች
ብለህ ብትናገር ብትጮሕ
ላንቃህ ደርቆ ማን ሰማህ ?
እውነት እውነት እያልክ ትጣራለህ
ወላጅ አባቱዋን እረስተህ
እስኪ አንጋጥ ወደሰማይ
አታገኛትም ከምድር ላይ
መስፈሪያ ስፍራ አጥታ
በአለም ክፋት ተሰላችታ
መደበቅም ሰልችቶዋት
ወስድአታል እና የላካት
አንጋጥ ወደእሱ ወደሰማይ
ፍርድን በቶሎ እንድታይ
በዚህም በዛም ለቅሶ
የስንቱ እንባ ፈሶ
ወዮላት ያቺ  ሀሰት
ማን ይናገራት ይሰራት
ዳንኪራ መታች በደስታ
የሰውን ውድቀት አብዝታ
ባዩሽ














Freitag, 22. August 2014

በገዛ ቤት መግቢያ ያሳጡኝ ወጣቶች፤





ይድረስ ለተቃዋሚ፣ ለገዢው ፓርቲም እና ለኢትዮጲያ ህዝብ


 ነጻ ፕሬስን አምንበታለሁ፡፡ በወቅቱ ጥቂት የነጻ ፕሬስ ጋዜጠኞች ሊያገለግሉኝ ያዳመጡኝ ነበሩእና፡፡ ነጻ ፕሬስ በአለም ላይ አለ፤በኢትዮጲያ የማይኖርበት ምክናያት ሞኝነት ነው፡፡ ይህ እከክልኝ ልከክልህ በሆነ ስራ አስፈጻሚ በሚፈራበት አገር፤ የነጻ ፕሬስ መኖር የሚጠቅመው ለገዢው ፓርቲ ነበር፡፡ ግን ያለማወቅ ጉዳይ ገዢው ፓርቲ ነጻ ፕሬስን አይፈልገውም፡፡ ለምሳሌ እከክልኝ ልከክልህ ያሉ ስራ አስፈጻሚዎች የመንግስትን ሚዲያ የተበደለው ህዝብ ክፍል እንዳይጠቀምበት አፍነው ይይዙታል፡፡ በዚህም የተነሳ ገዢው ፓርቲ ያልሰራውን ስራ ለማየት ሊቸገር ይችላል፡፡ ስለዚህ ነጻ ፕሬስ ግን ሲጽፈው፤ ያንን አንብቦ መንግስት ስራ አስፈጻሚውን ለምን ይህ ሆነ ተደረገ ብሎ መጠየቅ እና ለማስተካከል ይችልነበር፡፡ አሁን ግን በአንድ አገር ላይ ሁለት ዜጋ መፍጠር ማለት አንዱን እንደልብህ ሁን ሌላውን ተበደል ማለት ይሆናል፡፡  የእኔን ሕይወት የሰቆቃ አድርገውት የነበረው፤ እና ታላቅ የሆነ ስቃይ አስከትለውብኝ የነበሩትን ለመክሰስ አልቻልኩም፡፡ እነዚህ ሰዎች ያደረጉብኝን ስቃይ ለኢትዮጲያ መንግስት ፍርድ ቤት ከስሼ ለማስቀጣት ቀርቶ ለማስታገስ  እንኩዋን የምችልበት መንገድ በሙሉ የተዘጋ ነበር፡፡ ይህ የሆነበት ምክናያት ብዙዎቹ ስራ አስፈጻሚዎች  ሰንሰለታቸው  ከጥቅም አንጻር የተሳሰረ ስለነበር ነው፡፡ በተለይ ክፍለሀገር እኔ በነበርኩበት ወሎ ውስጥ ይህ መሰል ከባድ ፈተና የተጋረጠ ነው፡፡ ያለችኝን ገንዘብ አራግፌ ለመቁዋቁዋም ያደረኩት ጥረት ያተረፈልኝ ድህነትን፤ ኪሳራ እና የአይምሮ ቶርች ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ ቤተሰቤን ለመበተን ተገድጃለሁ፡፡ በውነቱ አውሬዎች ናቸው ጨካኞች ናቸው ክፉዎች ናቸው፡፡ የሴት ቤት ተበትኖ በእኔ ጫንካ እነዚህ ስራ አስፈጻሚዎችን መሸከም ማለት ዛሬ ሊያፍሩ ይገባቸዋል፡፡ ሰው ትንሽም ሰብአዊነት እንዴት እንደሚያጣ እጅግ በጣም ይገርመኛል፡፡ሴቶች ጉዳይ የምትባለውንም አንዲት ሴት ቀርቤ በደሴ ውስጥ ማለቴ ነው ባነጋግራት፤የእኔ ድርጅቴ ወርቅ ነው፡፡ አንቺ የድርጅቴ ተቃዋሚ ነሽ እያለች ልታዳምጠኝ አልቻለችም፡፡እኔም በማላውቀው ነገር እንደሚዳክሩ እና የሴቲቱንም ንብረት እያዘረፉ፤ ዘራፊያቸውን ለመተባበር ሲሉ ካለው ኢህአዴግ ጋር ጠላት አድርገው ሊያቀርቡኝ ወይም እንዳላተሙኝ  ተረዳሁ፡፡ ሰው ተቃዋሚ ከተባለ እንደላቀለት እና፤ ተስቦ እንደያዘው ሁሉ ሰው እንደሚሸሸው አውቃለሁ፡፡ ይፈራዋል፡፡  በዚህ ከእውነት ውጪ በሆነ ነገር ብዙ ተሰቃየሁ፡፡ ድፍን ዘጠኝ አመት የምሰራብትን እና ሰርቼም ግብር የማስገባበትን ቤት  በራፉን ለጋራጅ አሳልፈው ሰጡት፡፡ ባለጋራጁ እናቱ በወቅቱ የደሴ የሆነ ነገር ተመራጭ ስለነበረች የእኔን ክስ ሁሉ ከንቱ አደረገው፡፡ ይህንን ሁሉ ብዙው የደሴ ህዝብ ያውቀዋል፡፡ እንደእኔ እንባ እንደ ጎርፍ የወረደው ያለ አይመስለኝም፡፡ እንባ ጎርፍ ቢሆን ኖሮ የእኔ ብዙ ሰውን በወሰደ ነበር፡፡ ግን ገና አልሞላም መሰል መሰል፡፡ እንባዬ አንድ አካባቢ ላይ ባህር እንደሰራ አልጠራጠርም፡፡ የባለጋራጁም ግሩፖች፤ በራፌ ላይ በመቆም፤ ቀውስ እያሉ ይሰድቡኝ ነበር፡፡ በገዛ ቤት መግቢያ ያሳጡኝ ወጣቶች፤ እናታቸው እሆናለሁ፡፡ የአንተን እናት ለማትረፍ የሌላውን እናት ማጥፋት በአንዳንድ ጎረምሶች ተባዝቶ ይገኛል፡፡ ጥሩ ሲስተም ያፈራው ይሆን ጥሩ ወላጅ፤አዎ እዚህ ላይ ተምታቶብኛል፡፡ ሲስተም  ሴትን በማስለቀስ ? ምን ይጠቀም ይሆን?  ስለዚህ ስራዬን አቁዋርጬ ልጆቼን ወደጀርመን መለስኩኝ፡፡ ድህነት ባሪያ የማድረግ፤ ለማኝ የማድረግ ተጽእኖ ፈጣሪ ነውእና፡፡ የማበላቸው የመሰረትኩት ስራዬ በወንዜ ልጆች ተናግቶአል፡፡ ወንዝ በለኝ እንዲህ ነው፡፡ ሁሉንም አናጉት፡፡ የእነሱን ግን አቆሙት ወንድ ናቸውእና፡፡ ሴቶቻቸውም ባለወንድ ናቸውእና፡፡ በእኔ መውደቅ ሳቁ ተሳለቁ፡፡ አዎ ለጊዜው ሳቅ በሳቅ ሆነ፡፡ እነሱ አያፍሩም እኔ ግን አፈርኩላቸው፡፡  ጠበቃም ብፈልግ ማግኘት አልቻልኩም፡፡ ባለጋራጁንም ሆነ፤በፈራፌን  የሰጠውንም የቀበሌ ሊቀመንበር ፤እናቱ የምታገለግልበትን ቀበሌ ለመክሰስ አልቻልኩም፡፡ እንደእውነቱ ከሆነ ስቃዬ ሁሉ የጀመረው እነስዬ አብርሃ፤ እነታምራት ላይኔ ሁሉ በነበሩበት ግዜ ጀምሮ ነው፡፡ የእኔ እንጀራ ተዘግቶ ቤተሰቤ ተበትኖ ግን ያ ባለጋራጅ ወጣት ከብሮ አዲስአበባም ሆነ ደሴ እስከቤተሰቡ ድረስ ከብረው መኖር ጀምሩ፡፡ አዎ ምን ነበር ቢተወኝ፤ የተዋጣለት ባለሙያ ነበር፡፡ ሁሉ እጁን ይወደዋል፡፡ የትም ቢሆን ሰርቶ ማግኘት ይችል ነበር፡፡ አባት የለላቸውን ልጆች ሰርቼ ባሳድግ ምን ነበር፡፡ የኢትዮፒ አስከፊውን ገጽታ ማንም ሊያነሳው እና ሊጋፈጠው አይደፍርም፡፡ ግን እንዲሕ ነው ኢትዮጲያችን፡፡ እከሌ ጥሩ ሙስሊም ነው፤ እከሌ ጥሩ ክርስቲያን ነው ይባላል፡፡ በሁሉም ውስጥ ግን ኩነኔም እንዳለ ለማወቅ አንደፍርም፡፡ እውነት ከፈጣሪ ነው፡፡ እኔ ግን ሴት በመሆኔ ጉልበቴ ተሙዋጦ እንባ ብቻ የዠ ከስሬ፤ የነበረኝን ነገር እየሸጥኩ መብላት ጀመርኩ፡፡ እዚህ ላይ ባለጋራጁ ሙስሊም ልጅ ፈሪሃ እግዚአብሄር ቢኖረው ኖሮ፤ እረ ባዩሽን ይህችን ብቸኛ ሴት እኮ እየገፋሁዋት ነው ማለት በቻለ ነበር፡፡ እውነትን ለመረዳት ሀቅን ለመወጣት ሁሉም እምነት ያዛል እና፡፡ ይህቺ ሴት ካለባል ልጅ ይዛ እንዴትስ ሀቁዋን እነከላሁ ብሎ ባለመገመቱ ጭራሽ ግሩፕ እየላኩ ሕይወቴን የሰቆቃ ማድረጋቸው እስከአሁን ይገርመኛል፡፡ አዎ ያገሬ ሰዎች ድንቅ የሚለኝን ክፈሳቶች አይቻለሁ፤ ኖሬውማለሁ፡፡ ምንም እንኩዋን ለዚህ አይነት ህገወጥነት የጋበዘው የኢትዮጲያ መንግስት ስራ አስፈጻሚዎች ቢሆኑም የሰው ልጅ ፈጣሪ አለኝ እምነት አለኝ ስለሚል እምነቱ የሚለውን ቢዳስስ መልካም ነበር፡፡ ዛሬ እኔ እጅግ በጣም ተንገላትቼ እንደገና በጀርመን አገር እገኛለሁ፡፡ ኢሕአዴግ ጋር መፍተሄ ለማግኘት ያደረኩት ጥረት ሁሉ ከንቱ ሆነ፡፡ ሰውን የሚያንገላቱበት ስርአት በእራሱ መረጃ እንኩዋን ይዘህ የማታቀርብበትን መልክ እየቀየሩ መጡ፡፡ ሳስታውሰው ሰውነቴን ይወረኛል፡፡ ውስጤን ቅዝቃዜ ይጨምርበታል፡፡  ዛሬ ግን እኔም የምጠብቀው ፍርድ ነው፡፡ ፍርድ፤ ለኢትዮጲያ ህዝብ ጆሮ የሚደርስ ፍርድ፡፡ ብዙ የስነልቦና ተጽእኖ በማድረግ፤ ንብረቴ ሁሉ እንዲባክን ያደረጉትን ሰዎች ክስ ብመሰርትባቸው ደስ ይለኛል፡፡  ግን ይህ አሁን ባለው መንግስት አይቻለም፡፡ ለምን አይቻልም?  የእነሱ አባል ያለማጣት ፍላጎት ጉዳይ ይመስለኛል፡፡ ግን በዚህ አጋጣሚ ለሁሉም ልገልጥ የምችለው አንድ ነገር አለ፡፡ ኢትዮጲያ ወንበዴ አጥታ አታውቅም፡፡ የሴት ህይወት ግን እጅግ አዘቅት ውስጥ የወደቀ ነው፡፡ ይህ ህሊናውን የማይወቅሰው አድራስን ወዳድ በበዛበት አካባቢ የሚከሰጥ ነው፡፡ አንድን ሰው መንግስት እስኪወቅሰው መጠበቅ ባልነበረብን፡፡ ግና ቁስሌ ቁስሉ፤ ጭንቀቴ ጭንቁ፤ ችግሬ ችግሩ የሆነ ልቡ የራራ ሰው ማግኘት አልቻልኩም፡፡ ከቶም ተቃዋሚ በመባሌ ብቻ ሰው ከእኔ ጋር መሆን ፈራ ነበር፡፡ እኔ ለነገሩ አልነበርኩም፡፡ ግን ብሆን ኖሮ እራሱን ሰው ከእኔ በማሸሽ አዳነ ማለት ነው፡፡ አንድ ነገር ግን አውቃለሁ፤ እኔን ያስለቀሱኝ፣  የገፉኝ፣ እና ቤተሰብ እንድበትን ያስገደዱኝ ሁሉ ያካበቱትን አይበሉትም፡፡ ዘራቸውም እርጉም እንደሚሆን አውቃለሁ፡፡ እግዚአብሄር ይፈርዳል፡፡ እነዚህ ሰዎች ለእግዚአብሄርም ስራ እንቅፋት ናቸውእና ይፈርድባቸዋል፡፡ ግን ይህን ጥሁፍ የሚያነብ እና የሚያስተላልፍም ሁሉ መረዳት ያለበት ግን ፤ተቆጣጣሪ የለኝም እና መንግስትም እንደፈለገ ለቆኛል የሚል ትንሽ ህሊናውን ቢያመዛዝን መልካም ነው፡፡

ያነዬ ተቃዋሚ ናት ነፍጠኛ ናት እያላችሁ የምታስቸግሩኝ ሰዎች፤ እኔ ነፍጠኛ ከተባልኩ እናንተም ናችሁ፤ ምክናያቱም እናንተም ያሳደዳችሁኝ ትግሬ አልያም ኦሮሞ አይደላችሁም እና፡፡ ተቃዋሚ የምትሉኝ ግን ለመብላት ለመበዝበዝ እንዲመቻችሁ እንጂ እኔ እስከዛሬው ቀን ድረስ የማንም የፖለቲካ አባል ሆኘ አላውቅም፡፡ ብቃወምም ሰይጣናዊ የሆነን ተግባር፤ ሙስናን እና ማንአለብኝነትን ደግሞም እራስ ወዳድነትን ነው፡፡ የፓርቲ አባል ለመሆንም  አልፈልግም፡፡  ውነት የፓርቲ አባል ካልሆንኩ አንድ ፓፈርቲ ሊረዳኝ ካልፈለገ፤ ለእኔ ይህ ፓርቲ ሳይሆን አምባገነን ነው፡፡ እዛ በአባልነት ብቻ የሚረዳ ፓርቲ ጋር ምንም ግንኙነት ሊኖረኝ አይችልም፡፡ ለዚህ አይምሮዬ በቂ የሆነ እድገትን ይዞአል፡፡ይህ  ማለት ግን ነጻነቴን ያስገኝልኛል ማለት አይደለም፡፡ ፓርቲዎች ግን እዚሕ የሚገባው እድገት ላይ መድረስ ግድ ሊላቸው ይገባል፡፡  አባሉን ብቻ የሚንከባከብ ፓርቲ እድገቱ የተገደበ ይሆናል፡፡ በኢትዮጲያ አንዱ ፓርቲ ድምጥማጡ ካልጠፋ ሌላው መሪ መሆን የሚችል አይመስለውም፡፡ ይህ ሁሉ መታየት ያለበት ነገር ነው፡፡

አያችሁ ለመብቴ ለመቆም የግድ የፖለቲካ አባል መሆን የለብኝም፡፡ እንደእናንተ አይነት ምንግዜም ከኢትዮጲያ ይጠፋል ብዬ አልገምትም፡፡ ደፋ ቀና የምለው የግድ በኢኮኖሚ እራሴን ለመቻል ነበር፡፡ ግን ባል የለላት ሴት እንዳትቁዋቁዋም እንዳትሰራ የተከለከለበት አገር መሆኑን ሳላውቅ ኪሳራ ላይ ጥላችሁኛል፡፡ ይህ በእራሱ ያልሰለጠነ እስከአሁን ድረስ ደግሞ ከመካከለኛው ዘመን ሊወጣ ያልቻለ አመለካከት ሆኖብኛል፡፡  ይህ ሴትን የሚጫን ሁዋላ ቀር አስተሳሰብ እንዲቀር ባለኝ አቅም ግን እታገላለሁ፡፡ መቼም ሰውን መግደል አልያም ማሰር እንጂ መልስ የሚሰጥ ወይም ከወደቀበት ሰውን የሚያነሳ በአገሬ አንድ ሀይል መፍጠር እንዳልቻልን ሁሉም ልቦናው ያውቀዋል፡፡ ሰውም ታፈራለች  ብዬ በበኩሌ መገመት አቅቶኛል፡፡ ምንአልባት ስቃዬ እይታዬን ሸፍኖት ሊሆን ይችላል፡፡ ሰው ሆዱን ከተመለከተ አገሩ ወገኑ ትዝ አይለውም እና፡፡ በድጋሜ የምለው እስከአሁን የተቃዋሚ ፓርቲ አባል አይደለሁም፡፡ ያዘረፋችሁኝ ያስለቀሳችሁኝ ደግሞም ያሳደዳችሁኝ ለእራሳችሁ ኪስ ስትሉ እንጂ እኔ ለመሰደድ ምክናያት ለመበደል ምክናያት ኖሮብኝ አልነበረም፡፡ እኔ ኢሕአዴግ አባል አይደለሁም ማለት ተቃዋሚ ፓርቲ ውስጥ አለሁ ማለት አይደለም፡፡ ደግሞም ሁሉም የግድ የፓርቲ አባል መሆን የለበትም፡፡ እኔ ግን አንዲት ሴት ነኝ፡፡ ያስለቀሳችሁት የበተናችሁት የአንዲት ሰላማዊ ሴት ሕይወት ነው፡፡ ይህ እግዚአብሄር ይፋረዳችሁ፡፡ ይህ ሁሉ ሊያሳፍራችሁ እና ሊያጸጽታችሁ ይገባል፡፡ ለኢትዮጲያ አልያም ለፓርቲው ተቆርቁራችሁ እንዳልሆነ ለማወቅ የተሳነኝ ደንቆሮ አይደለሁም፡፡ እናንተም ይህንን ስሙን ማስፈራሪያ አድርጋችሁ የምትጠቀሙበትን ኢሕአዴግን ገደል አፋፍ ላይ እንዳቆማችሁት ሊገባችሁ የሚችል ምንም ግንዛቤ የላችሁም፡፡ ኢሕአዴግ ከሰማሕ እና ከገባህ፤ ደሴ ላይ እስር ውስጥ ተወርውሬ ነበር እና ለምን እንደታሰርኩ እና ማን እንዳሰረኝ ለማጣራት ትችላለህ፡፡ ስህተቶች እንዴት እየተፈጸሙ እንዳሉ አስተውል፡፡ ሰውም ለምን ወደተቃውሞ መሄድ እንደሚገደድ ተረዳ፡፡ ሰው የእራሱን ህይወት በሰላም ለመኖር ግድ ጥያቄ ማቅረቡ አይቀርም እና፡፡ አራተኛ ፖሊስ ጣቢያ እና ደሴ ወረዳ ፍርድ ቤት ያለውን እና ደሴ ቀበሌ 10 ቡዋንቡዋ ውሃ ያለውን ሁኔታ ማጣረት እናመገመት ይቻላል፡፡ በደሴ ኢምግሬሽንም ተገኝቼ እርዳታ እንዲያደርጉልኝ እና በእኔ ላይ የሚደረገው ዘመቻ እንዲቀንስልኝ ብዙ ጥረት አድርጌአለሁ፡፡ ግን ምክናያቱን ባልተረዳሁት መሰረት  የሰቆቃ እንባ አልቅሼ ወጥቻለሁ፡፡ ይህ ብቻ አይደለም ብዙ ጉዳዮች አሉ፡፡? አልፈልግም፡፡ እኔም እንደማንኛውም ሰው የመኖር መብት እንዲከበርልኝ እና ጉዳዮቼ የህግ ምላሽ እንዲያገኙ እንጂ፡ በዚህም የተነሳ ትግሌን በዚህ መልኩ እቀጥላለሁ፡፡ እኔ ሴት ነኝ፤ ኢትዮጲያም ለመኖር የግድ የወንድ መከታ ወይም የፖለቲካ ፓርቲ መከታ የሚስፈልገኝ መሆን የለበትም፡፡ የሚያስፈልገኝ የህግ የበላይነት እንጂ፡፡ ኢሕአዴግ አሁን ያለሕ በአገሪቱ ውስጥ አንተ ብቻ ነሕ፡፡ በአንተም ጊዜ ብዙ የተደጋጋመ ግፍ ደርሶብኛል፡፡ በፍርሃት እና በሰቆቃ የሚገባኝ ህግ መጠቀም  ባለመቻሌ ቁሳዊም ሆነ አካላዊ ጉዳት ደርሶብኝ ከአገር ወጥቼለሁ፡፡ ወጥቻለሁ ማለት ግን አልመለስም ማለት አይደለም፡፡ ማንኛውንም የፖለቲካ ፓርቲን ፈልጌ እንዲህ ሆንኩ ብዬ አልለውም፡፡ ሁሉም የጠጠመደበት ሪዮተ አለም አለውእና፡፡ ግን ችግሮቼን ባገኘሁት ሚዲያ ፌሴ ቡክ ላይ በተደጋጋሚ አቅርቤአለሁ፡፡ ለሰብአዊነት አለሁ የሚል አካል ወይም ተደማጭነት ያለው ሚዲያ ወይም ጋዜጠኛ ሁሉ  ሊገናኘኝ ይችላል፡፡ ለጥያቄዎቼ መልስ ለችግሮቼ መፍተሄ እሻለሁ እና፡፡ ለነገሩ በኢትዮጲውያኖች እጅ ያለ ሚዲያ ሁሉ  ግልጋሎቱ የሚውለው ለዲሞክራቲክ ለሆነ ነገር ሳይሆን ላመኑበት ጉዳይ ብቻ ልምድ የካበተ ባህል ውስጥ ያለ እንዳሆን ፍርሃቱ አለኝ፡፡ ይህ በብዛት የርኢዮተ አለም ማራመጃ የሆነ ሚዲያ ሰብአዊነትን ይመለከታል ብዬ ለማመን እቸገራለሁ፡፡ በዚህም የተነሳ የነጻ አገልግሎት የሚሰጡ ሚዲያዊች በተለይ ለሴት አምድ የሚሰጠው ሎሚ መጽሄት በመሰደዱ አዝናለሁ፡፡ የሎሚ መጽሄት አዘጋጅ አቶ ግዛቸውን በዚህ አጋጣሚ ላመሰግነው እወዳለሁ፡፡ አጥንት፣ዘር፣ ደግሞም ሀይማኖት እና ጾታ ወይም የፖለቲካ አቁዋም ሳይጠይቅ  ሚዲያውን እንድንጠቀም እድል ሲሰጥ ተመልክቻለሁ እና፡፡ በሳውዲ አረቢያ ያሚንገላቱትን ሴት እህቶችም ችግር እና ሰቆቃ ብዙ ይጽፍ ነበር፡፡ በቸር ባዪሽ

Donnerstag, 21. August 2014

ሁልግዜ የሚያንቀሳቅስህ ሃይል ፈላጊ አትሁን፡፡







አንዳንዶች ፌስቡክን እንደሚያጠፋቸው በመቁጠር ሊያጠፉት ይጥራሉ፡፡ ወጣቶችን ይከለክላሉ፡፡ ፌስ ቡክ እንዲሕ መጥፎ ቢሆን ኖሮ በኢዮሮፕ የፈረንጁ ወጣት፤ ለይኑቨርሲቲም በቅቶ ለአገሩ ትርፋማ ባልሆነ፡፡ ሌላውም የዲሞክራሲን እድገት ተቀብሎ በአገራቸው ልማት  ባልተሰለፈ፡፡ ወጣቱ በሙሉ ማለት ይቻላል የፌስቡክ ተጠቃሚ ነው፡፡ ጊዜውንም በከንቱ ነገር አያባክነውም፡፡ እንዳውም ብዙውን ግዜ የሴክስ መሰል ነገር የሚጠቀሙት ወጣቶች ሳይሆኑ፤ ሌላ ችግር ያለባቸው፤ ሴት ማግኘት የማይችሉ እና የሆነ የጤና ችግር ያለባቸው ናቸው፡፡ ዛሬ የአለምን ህዝብ ባህል እና ማንነት እያስተዋወቀ እንዲቀራረብ እና ዘረኝነት ከሰዎች አይምሮ ቦታ እንዲያጣ እያደረገው የሄደው፤ የፌስ ቡክ ግንኙነቶች ያመጣው እድገት ነው፡፡ ፌስ ቡክ ከፈለክ ጠቃሚ የሆነ ነገር በመመልከት በመምረጥ እና እርስ በእርስም በመነጋገር አይምሮን ለሚያሳድግ ነገር መጠቀም ይቻላል፡፡ ፌስ ቡክ የፈረንጆችን ወጣቶቻቸውን የሚገል ቢሆን ኖሮ  ደዝባውን ባጠፉት ነበር፡፡ ዛሬ የአለም ህዝብ በማንኛውም አገር ከሚኖሩ መሰል ባህሪ ካላቸው ሰዎች ጋር አስተሳሰብን ይጋሩበታል፤ ይካፈሉበታል፡፡ የአለም ሳይንቲስቶች መገናኛም መተዋወቂያም ሆኖአል፡፡ እንዳውም ባህሪ ለባህሪ ለመተዋወቅ ሰፊግዜ የሚሰጥ የፌስቡክ ግንኙነቶች መሆናቸው በሰፊው እየተነገረ ነው፡፡  ስለዚህ መልእክቴ ለእኛ አገር ሰዎች፤  ፌስቡክን የማይጠፋውን ለማጥፋት ከመታገል፤ ወጣቱን ፊስቡክን ለምን እንደሚጠቀሙበት አይምሮን አስፍቶ መሪ መሆን ያስፈልጋል፡፡ያደነቆርከው ወጣት ለእራስህም ጥቅም የለውም እና አባትነትህንም ይክደዋል፡፡ ያጠመድከው ወፍ አንድ ቀን በር ቢያገኝ በራሪ መሆኑን አትዘንጋ፡፡ ሌላው ፌስ ቡክ ላይ የምትገናኙትን ሰው ቀድማችሁ አትመኑ፡፡ ምክናያቱም ብዙም አይምሮአቸው በርካሽ ነገር የወደቁ ሰዎች ይጠቀሙበታል እና፡፡ ዛሬ የሰለጠነው አለም ላይ የሚኖሩ ሰዎች ፌስቡክንም ሚስቶቻቸውን እና ባሎቻቸውን ለመምረጥ ይጠቀሙበታል፡፡ እንዳውም ፊት ለፊት በቶሎ የምታገኘው ሰው ጋር መገናኘት፤ በሳል የሆነ መተዋወቅ ሳታደርግ ፤ ዘሎ ወደጋብቻ አልያም  ወደግብረስጋ ግንኙነት በመገስገስ፤ ያልተፈለገ ልጅ ወይም ያልጠበከው ትዳር ውስጥ አዝፍቆ ሲያጨቃጭቅህ ይኖራል፡፡ ለማንኛውም ወሳኝ አብሮነት፤ በትዳርም ሆነ በፖለቲካ አስተሳሰብ ወሳንነት አለውእና፡፡  በፊስ ቡክ ግን የምትተዋወቀውን ሰው፤ በቶሎ ስለማታገኘው የሰፋ የመተዋወቅ ጊዜ በምታደርጋቸው የረጅም እርቀት ንግግር አትራፊነትም አለው፡፡ በፋስ ቡክ ሁሉም ስለእራሱ የሚፈልገው የፖለቲካ ፓርቲ በሰፊው መነጋገር መጨቃጨቅ እና መረዳዳት ይችላል፡፡ የሰውን አስተሳሰቡን ለመረዳት ወይም የተለየውን አስተሳሰብ ለማቀራረብ፤ እረጅም ውይይት ወሳኝነት አለው፡፡ ዛሬ በፌስ ቡክ መገናኘት የሚመሰረተው ትዳር በኢይሮፕ  ትልቁን ቁጥር የያዘ ሆኖአል፡፡ ይህም የዘንድሮን ጋብቻ ሰፋ ያለውን ስፍራ እንዲሸፍን አድርጎታል፡፡ በፌስቡክ የሚመጣውንም የአገር ገቢ ኢንቬስትሜንት ትርፋማ አድርጎታል፡፡ ዛሬ አንዱ አሁግር ከሌላው ጋር የሚያደርገው የፌስቡክ ትውውቅ መንገድ፤ ሰውን ከዘረኝነት መንፈስ እያወጣ ግሎባል የሆነ ማይንድ የማስያዝ አቅሙ ከፍተኛ ሆኖአል፡፡ ስለዚህ ፌስ ቡክን ለሚገባ ነገር በመጠቀም ለተለያዩ የአስተሳሰብ እድገት እና አብሮ የሚያስኖረውን የዘረኝነት ጠላት የሆነውን አለምን በመቅረብ ተማማሩ፡፡ ለማንኛውም ፖለቲካም አስተሳሰብ ሆነ ማህበራዊ ህይወት ለመጠናከር ወጣቱ ትዳርም እጅግ በጣም አስፈላጊ መሆኑን እና የጠንካራ ቤተሰብ መመስረቻ ነውእና ንቃችሁ ማየት የለለባችሁ አንዱ የህይወታችሁ ክፍል መሆኑን አትዘንጉ፡፡ ትዳር አላማን የማያጠናከር ይህ ነው የማይበል አስተዋጽኦ ያለው ነው፡፡ መነጋገር እና መተዋወቅ እና በአስተሳሰብ መቀራረብ እንጂ ሀብት የጥሩ ቤተሰብ መመስረቻ መሰረት ሊሆን አይችልም፡፡ ካለጠንካራ ቤተሰብ ለአገርእና ለእኩልነትም መታገል ውድቀት ያመጣል፡፡ እኔ የምናገረው ምንአልባት እኔ ካጠፋሁት እና ከተሳሳትኩት ነገሮች በመነሳት ይሆናል፡፡ ሕይወት በእራሱ የማይቁዋጭ/ መጨረሻ የለለው/ ዩንቨረሲቲ/ ነው፡፡ ጠባብእነት አካባቢን ከመበከል አልፎ የእራስንም ሕይወት የማበላሸት ሃይል አለው፡፡ ስለዚህ ልብ የምትሉትን ልብ በሉእና ግዜአችሁን በከንቱ አታሳልፉት፡፡  የፖለቲካ ጉዋዶቻችሁ እና መሰሎቻችሁንም ለመፈለግ ፌስቡክ ትልቅ አስተዋጽኦ አለው፡፡ እናንተ በፌስ ቡክ ላይ መናገር ያለባችሁ የምታምኑበትን እንጂ የማታምኑበትን አታውሩ፡፡ ይህ በእራሱ ወላዋይነትን ያመጣል እና፡፡ ለማንኛውም እርምጃ ድፍረትን ይጠይቃል፡፡ አይምሮን ከሚገል የባህል ትብታብ መውጣት ለእራስ እድገት ትልቅ ወሳኝነት አለው፡፡ የእራስህ የአስተሳሰብህ ውሳኔ ከለለህ ፈረሱ ለሚጎትተው ጋሪ ተሸከርካሪው ጎማ ትሆናለሕ፡፡ ጎማ ካለፈረስ ጉልበት ዋጋ የለውምእና፡፡ ሁልግዜ የሚያንቀሳቅስህ ሃይል ፈላጊ አትሁን፡፡ በቸር የምላችሁ ባዩሽ ነኝ፡፡