ኢትዮጲያ በብሄር ብትከፋፈል፤ ኦሮሞው ከደቡብ ህዝብ፣ ከአማራው፣ ከጉራጌው እና ከአካባቢውም ትንንሽ ብሄሮች ጋር ሰላም አይኖረውም፡፡ ስለዚህ አካባቢው ሁሉ እንደፓልስቲያን እና እስራኤል ልጆች፤ ልጆቻችሁ እርስ በእርሳቸው አካባቢውን ዲንጋ መወራወሪያ ያደርጉታል፡፡ ከመዋለድም አልፎ የድንበር ከለላው አስቸጋሪ ይሆናል፡፡ ትግራይ ግን ከራያ በላይ ያለውን ግራካሶ ገደል አልፎ ዲነጋ መወርወር ስለማይቻል፤ የትግራይ ነባር ክልሎች በሰላም ይኖራሉ፡፡ ይሁንእና ግን፤ የትግራይ ህዝብ ወደመሃል ኢትዮጲያ እንደልቡ መጉዋዝ እና የፈለገውን እህል እና ጥራጥሬ ሸምቶ ለመመለስ አይችልም፡፡ ይህ የሚሆንበትም ምክናያት፤ ውሎ አድሮ ለብሄር መተራመስ በወያኔ የተነሳ በትግራይ ህዝብ ላይ የሚኖረው አመለካከት የደፈረሰ ስለሚሆን ነው፡፡
የመገዛት ትእግስት ፡፡---- አገሪቱ ብትገነጣጠል፤ አማራው አካባቢ ሰላም ይሆናል፡፡ ይህም የሚሆንበት ምክናያት፤ የአማራው ህዝብ የማተርያል ጉጉት የለለው እና፤ በአንድ ልብስ ብዙ አመት መኖር የሚችል እና ካለጫማም መሬትን የሚደፍር ስለሆነ ነው፡፡ ይህም ደግሞ የሚሆነው ለእምነት የተገዛ ሙስሊም እና ኦርቶዶክስ፤ አምላኩን ተስፋ አድርጎ የሚኖር ልምድ ያካበተ በመሆኑ ነው፡፡ ለዚህም መረጃዎች በአማራው ክልል የሚገኙ ገዳማት ሲሆን በገዳሙ አካባቢ የሚኖረው ነዋሪ ህዝብም ንዋይ ሰፍ የማያደርገው በመሆኑ ነው፡፡ አማራው ህዝብ ለህግ መገዛቱም፤ እና ለሰላም ለአንድነት በባዶ ኪሱ መጣሩ በእራሱ ለአካባቢው ሰላም አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡ ለምሳሌ ወያኔ ኢሕአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ ወዲህ፤ በአማራው ላይ ያለፈው ስርአት ገዢ፣ በዳይ እና ጨቁዋኝ እየተባለ እንደተፈረጀ እና ፤ የዘመናት ጥፋት በዚህ ብሄር ላይ እንደተጠቃለለ የ24 አመቱ ሲወራ ሲዘከር የነበረው ታሪክ መረጃ ነው፡፤ ይሁን እና ግን አማራው ደግሞ ከማንኛውም ዘር የበለጠ በትምህርት ቤትም ሆነ በኢኮኖሚው ከሌላው ክልል የተሻለ እና፤ የተለዬ ተጠቃሚ ያደረገው ምንም አይነት መረጃ አልተገኘም፡፡ አማራው ግን አንድነት ሰላም ነው ብሎ ደምድሞ ይዞ እየተጉዋዘ ነው፡፡ ይህም መረጃ የሚሆነው፤ ወደፊትም ኢትዮጲያ ብትገነጣጠል፤ አማራው ለተሰጠው ጥዋ ሰላሙን እና አስተዳደሩን አስተካክሎ መኖር ይችላል፡፡ የሚቀርበት ከሌላው ብሄር ጋር የሚለዋወጠው ፍቅር ብቻ እንጂ፤ ንዋይ ሊሆን አይችልም፡፡
ወጣቱ፡፡------ኢትዮጲያ ብትገነጣጠል ያለፉት መንግስታቶች እስከመንግስቱ ሀይለማርያም ድረስ ይመሰገናሉ ይወደሳሉ፡፡ ምክናያቱም በመከፋፈል ሰላም አይኖርም፡፡ ትውልዱም ያለፈውን ታሪክ ሲሰማ የተገነጣጠለበትን ዘመን ግን ይረግማል ይወቅሳል ይጠላል፡፡ ሰላም ይናፍቀዋል እና፡፡
እምነት፡፡-----ፔንጤ በኢትዮጲያ ውስጥ የገነነው በወያኔ ኢሕአዴግ ዘመን ነው፡፡ በዚህ በወያኔ ዘመን፤ ስለዘር ወይም ብሄር የሚባልበት ገኖ በሚወራበት አዲስ ዘመን ፤ የፔንጤ እምነት ተከታይ የሆኑ ባለስልጣናት እና ስራ አስፈጻሚዎች የሚገኙበት እና በአስተዳደሩም የተካፈሉበት ወቅት ነው፡፡ ይህ አዲስ የሆነ ነገር፤ ብዙ ፔንጤዎችንም ይህንን አሁን ያለውን አስተዳደር እንደሚደግፉ በሰፊው ይነገራል፡፡ ደግሞም ሰው ነጻነቴን አግኝቸበታለሁ የሚለውን ስርአት መደገፉ ትክክል ቢሆንም፤ ግን የሁሉንም መብት እኩል ያልጠበቀውን ስርአት መደገፍ በብዙዎች ላይ ልዩነት እንደፈጠረ የማንክደው ሀቅ ሆኖአል፡፡ ስለዚህ የምንኖርበት አካባቢ ሰላሙን ለመጠበቅ ሁሉም በመብቱ እኩል መስተናገድ እንደሚኖርበት፤ የሰው ልጅ ሁሉ ለሌላውም መቆም አለበት፡፡ ኢትዮጲያ የሁሉም ዘር እና ሃይማኖት እኩል መስተናገጃ ካልሆነች ሁከት እንጂ ሰላም አይኖርም፡፡ እንደአማኝ ስናስብ፤ ለእምነት የአካባቢ ሰላም ወሳኝ ነው፡፡ ስለዚህ እኔን ተመችቶኛል እና ለሌላው ዴንታ የለኝምም ማለት አንችልም፡፡ አልያም ትናንት እኔ ተገፍቻለሁ እና፤ ዛሬ እኔ ሌላውን ልግፋም ማለት ሀጢያት ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ኢትዮጲያ በተጋረጠባት የብሄር ክፍፍል እውን ሆኖ ብትገነጣጠል፤ ፔንጤ በኢትዮጲያ ውስጥ ፈታኝ የሆነ ግዜ ሊገጥመው ይችላል፡፡ ብዙ የቤተክርስቲያን አባል ሊያጣ ይችላል፡፡ ይህን የሚያደርገውም፤ ኢትዮጲያ ብትከፋፈል የአካባቢው ሰላም ስለሚደፈርስ ነው፡፡ በብሄር የተነሳ አገሪቱን መከፋፈል የሚያመጣው ትርፍ፤ የተዋለደው የጉላላል፤ ከየአካባቢውም ይገለላል፡፡ የወሰን ክፍፍሉም አካባቢውን የጦርነት አውድማ ያደርገዋል፡፡ በዚሀወም የተነሳ ወጣቶችም አብረው እንዳይውሉ የሚያደረግ የመበቃቀል ሁኔታ ይከሰታል፡፡ ስለዚህ ፔንጤ የሆነ ሁሉ ይህ የብሄር ክፍፍል እውን እንዳይሆን እና ኢትዮጲያ እንዳትገነጣጠል የፍቅር ስበካውን ሁሉም በየብሄሩ ማስተናገድ እና፤ የአንድነት ጥቅምንም ማስረዳት አለበት፡፡ በአካባቢው የሁሉ ግንዛቤ እኩል ስላልሆነ ይህ ከመሆኑ በፊት ቀድሞ አገሪቱን መጠበቅ ግድ ይላል፡፡ ክርስቶስ ሰላም ነው፡፡ ክርስቶስ ፍቅር ነው፡፡ አገሪቱ ድህነት ቢኖራትም፤ ኦርቶዶክስ እና ሙስሊሙ እስከአሁን ምንም ንዋይ ሳይበግረው በሰላም እና በአንድነት አገሪትን ጠብቆዋት ኑሮአል እና፡፡ ሰው ይጠፋል ያለው፤ ይለመልማል፡፡ ሰው ያገነነው ይወድቃል፡፡ አንድ አገር የገነነ ነገር ስትሰራ የመውደቁዋ ምክናያት ይሆናል፡፡ አንድ መሪ ፎቶውን እና ሀውልቱን ሲያቆምም ይቀሰፋል፡፡ ቤተክርስቲያን ልትጠለፍ ትችላለች፡፡ አንተ ግን የእራስህ በመሆንህ ለእግዚአብሄር እውነት ተውስናለህ፡፡ በልብህ ውስጥ ያለውን ማን ይጠልፋልእና፡፡ያለፈው ዘመን የኦርቶዶክስ እና በሙስሊሙአንድነት ያለፈ ይመስላል፡፡ የዛሬው ደግሞ በአዲስ ተተክቶአል፡፡ አዲሱ ያለፈውን በየት ላግኘው የሚያስብል ሊሆን ይችላል እና፡፡
ሁላችንም የኢትዮጲያን አንድነት የምንፈልገው ከሆነ፤ ስራ መስራት ይጠበቅብናል፡፡ የማንፈልገውም ከሆነ ሁሉም የእራሱን ፍላጎት ይጠይቃል፡፡ አሁን ወያኔ ጥሩ ነው መጥፎ ነው የሚለው ሳይሆን፤ በአገሪቱ ውስጥ ያለው ክፍተት ከየት ወደየት እየወሰደን እንደሆነ ማስተዋል ግድ ይለናል፡፡ እምነት ላላቸው ሰዎች ሁሉ በአገሪቱ ውስጥ ፖለቲከኞች ተቀራርበው የሚሰሩበትን አጀንዳ እንዲከፍቱ ማስገደድ ግድ ይለናል፡፡ አገሪቱን ማዳን ማለት ሰላምን መጠበቅ ነውእና፡፡ ፖለቲከኞች አንድ ቀን ከስልጣን ይለያሉ፡፡ ግን ትተውልን የሚያልፉትን ቀውስ ለትውልዱ እንደእርግማን መተው እና መሄድ የማይገባን እኛ ሕዝብ ነን፡፡ ጦርነት የረሳው እና የማያውቀው ትውልድ ጦርነትን በአገሩ አሳልፎ በየሰፈሩ እንዳይሆንበት፤ ለአንድነት፤ ለዲሞክራሲ ፤ ለሰላም መወሰን እና ማስተዋል አለበት፡፡
ባዩሽ