Samstag, 1. August 2015

አንድ ለአምስት፤ በሰው አይምሮ ውስጥ


ስትወድቅ የጣለኝ ምንድን ነው በል፡፡ እሱንም እወቀው፡፡ የጣለህን ነገር ሳታውቅ፤ የጣለህን መላቀቅ አትችልም፡፡ እራስህን ለመርዳት ጥረት አድርግ፡፡ ከሌላው ከጠበክ እሱ የበለጠ ጉልበት ያስወጣሃል፡፡ ጠላትህን አትጉዳው፤ ግን ደጋግሞ እንዳይጎዳህ፤ ሽሸው፡፡ ለመሸሽ ግን መጀመሪያ የጎዳህን ሜተዱን/የመጉጃ መሳሪያውን እወቅ፡፡ ሰው እራሱን ለማትረፍ ጥበብ ተሰጥቶታል እና፤ መንገድህን ይዘህ ሂድ ቀጥል፡፡ ሰው ምንግዜም የሚለው አያጣም እና፤ ወደሁዋላ አትመልከት፡፡ 

 ሞት ሞት እንዲሸትህ የሚያደርጉ ሰዎች በአገራችን ጥቂት አይባሉም፡፡ እንግዲህ ባህሪያቸውን ልንገርህ እና ከእነሱ እራስህን አሽሽ፡፡ ቢቻለህ በሮኬት፣ አልያም በመኪና፡፡ ባይቻልህ በፈረስ ሽሽ፡፡ ይህ ሁሉ ካልተቻለህ፤ መንፈስህን አሽሸው፡፡ ባህሪያቸው፤ ጉሮኞች፣ ውሸታሞች፣ ሸንጋዮች፣ ድግስ አብዝተው ሰው የሚጋብዙ፣ ማህበራዊ ህይወት ላይ ተፍ ተፍ የሚያበዙ፤ ስውር የክፋት አጀንዳ የሚያራምዱ፣  ሰውን  አግለው የሚያስገልሉ፣ የባለስልጣን እና  የተዋቂ ሰው ስም እየጠሩ እከሌን አውቀዋለሁ እከሌ ዘመዴ ነው  የሚሉ፡፡ ስጦታ መስጠት የሚያበዙ፣  ደግሞም ስትመለከታቸው፤ በእራስ መተማመን የገነቡት፤ ከእነሱ በቀለም ትምህርት አንሶ ያዩትን በግሩፓቸው ውስጥ በመሰብሰብ ነው፡፡ ከእነሱ በእውቀትም ሆነ በኑሮው ያነሰውን ሰው በመሰብሰብ፤ እራሳቸውን ትልቅ በማድረግ እንዲወራላቸው እና ዝነኛ ሆነው እንዲቀርቡ የማድረግ ጥበብ አላቸው፡፡  የእነሱ የሸር ጥበብ  ወጥመድ ውስጥ የወደቁ አጫፋሪዎች፤ ሰውየው የፈለገውን ክፉ ቢሆን እና ስውር የሆነ አጀንዳውን ሊያቁበት አይችሉም፡፡ ይገርማል፡፡ እነዚህ ሰብስቦች፤ ይህ በማሀበራቸው ደምቆ ተፍ ተፍ ተብሎ በእነሱ አንቱ የተባለ ሰው፤ እንኩዋን እነሱ የሰውየውን ስውር አጀንዳ ሊያቁበት ቀርቶ፤ እንዳውም ጥሩ ሰው መልካም እየተባለ እንዲመሰገን እና ስሙ እንዲገን ያደርጉታል፡፡ ይህ የንቃተ ህሊና ድክመት እና የግንዛቤ እጠረት የሚከሰተው ብዙውን ግዜ በሴቶች ውስጥ ሆኖ አይቸዋለሁ፡፡ ለምሳሌ ያቺ ሴት በአስተሳሰብም ሆነ፣ በመልክ አልያም በትምህርት ሆነ በተለያዬ እሱዋ እራሱዋ ትበልጠኛለች ባለቸው ነገር የተናደደች ሴት፤ የአንድ ሴትንም ስም ለማጉደፍ ለማግለል የግድ ተወታትረው በቤተክርስቲያን ወይም በበጎ አድራጎት አልያም በሌላ ነገር ተሳቦ ማህበር ሊያቁዋቁሙ ሲውተረተሩ አያለሁ፡፡ ተመልክቻለሁም፡፡  ይህ አላማው የጠላችውን ወይም በተለያየው እይትዋ ትበልጠኛለች ያለችውን ሰው ወይም ሴት ለመጉዳት የታቀደ አላማ ብቻ ነው፡፡ ብዙ ግዜ ፖለቲከኞች ብቻ አይደሉም አንድ ለአምስትን የሚመሰርቱት፡፡ ይህንን ለመመስረት የአንዳንድ ሰዎችም መርዛማ ባህሪ አስረጂ መሆኑን አረጋግጫለሁ፡፡ 

 
              እዚህ ማህበር ውስጥ በምንም ታአምር፤ የማሃበሩ አለቃ የሆነቸው ባለስውር አጀንደዋ፤ መጀመሪያ የምትነዛው ፕሮፖጋንዳ፤ የጠላቸውን ሰው ስም በማጥፋት እንድትገለል እንዳትታመን  የሚያሰደርጋትን ወሬ በየተራ ለሰዎች በየግላቸው ከነዛች በሁዋላ ነው፡፡ ልብ በሉ ማህበር ውስጥ የአንድ ሰው የጥላቻ ነገር በጅምላ በአዋጅ አይታወጅም፡፡ ልብ ብላችሁ ስትመለከቱ፤ የአንድ ሰው እርኩስ ምግባሩ፤ ለማህበር ያጨውን ወይም ሊያሰባስባቸው ያቀዳቸውን ሰዎች፤ በየተራ እቤቱ በዶሮ ወጥ በጥሬ ስጋ እና በታላቅ ክብር ግብዣ እየጠራ እያበላ ነው  ስውር አጀንዳውን የሚያስተላልፈው፡፡ መርዙን የሚረጨው፡፡ ብዙ የሚገርሙ ነገሮች አይቼ ለመታዘብ የረዳኝን አምላክ ስሙ የተባረከ ይሁን፡፡ ሰውነታቸውን ስብእናቸውን ግን በምግብ ብቻ በሆዳቸው ብቻ እንደሸጡት ያልገባቸሰው ሰዎች፤ ፍጹም የማያውቁት ሰው ስም ሲጠፋላቸው፤ አምነው ተቀብለው የበሉትን የቅቤ እና የበርበሬ ጠረን እያገሱ፤ አይ ዶሮ ወጥ እያሉ ይወጣሉ፡፡ ከዛም የተነገራቸውን የሀሰት ቫይረስ እነሱም አስተጋቢ ይሆናሉ፡፡  ይህም ነው በአገራችን ፍርደገምድልነት እያደገ፤ በቀበሌውም በፖለቲካውም ገብቶ የሚያምሰው፡፡ 

              ብዙ የተለያዬ የህይወት ልምድ ብወስድም፤ በአንድ በኩል ግን ለምንድን ነው እከሌ እከሌ ከእኔ የራቁት በማለት ነገሩን ኮስተር ብዬ መመልከት ጀመርኩ፡፡ ሰውን ማኩርፍ አልፈልግም፡፡ ለማኩረፍ በቂ ምክናያት ቢኖረኝም፡፡ እኔ ግን ሁኔታዎችን መሰረቱን ማወቅ እፈልጋለሁ፡፡ የሚገርመኝ የጎዱኝ ሰዎች በጣም ህይወቴንም ገንዘቤንም ሆነ ጉልበቴን እና ፍቅሬን የሰጠሁዋቸው እና ይሆኑኛል ብዬ የመረጥኩዋቸው ያገለገልኩዋቸው ሰዎች መሆናቸው ነው የደነቀኝ፡፡ ስለዚህ ጌታ የረዳኝ በደንብ መሰረቱን እንዳውቀው እንድመራመርበት ይመስላል እማይቀየም ፣እማትከፋ  እና ቻይ አድርጎኛል፡፡  ስለዚህ የሚጎዱኝን ሰዎች ደጋግሜ መገናኘት ግድ ይለኝ ነበር፡፡ ሞኝም ያስመሰለኝ ይህ ባህሪዬ ነው፡፡ በእርግጥም እነዚህ ሰዎች የበለጠ እየናቁኝ፤ በእኔ ውድቀት ግን እራሳቸውን እየገነቡ፤ ልባቸው እና ሰውነታቸው እያበጠ ሲሄድ አየው ነበር፡፡ መቸም ሰውን ሰው የሚጎዳው የአስተሳሰብ አይምሮው ሚዛኑን ያልጠበቀ ነው ብዬ ከልጅነቴም አምናለሁ፡፡ እዚህ ላይ የምትረዱልኝ ነገር፤ እኔ ከሁሉም ተሸዬ እና አልያም የተሻለ እውቀት ኖሮኝ ሳይሆን፤ ብቸኝነቱ እና የተደረገብኝ የስም ማጥፋት ዘመቻ፤ ስለመረረኝ እና አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ስላደረሰኝ እና ጉዳት ስላመጣብኝ ነው፡፡ እግዚአብሄርንም እንድወደው ያደረገኝ የማይተወኝ እና የሚቆምልኝ  በከተማው ውስጥ የማደርገውን የበረሃውን  ጉዞ እንዳቁዋርጥ የሚረዳኝ እሱ ብቻ ሆኖ ስላየሁት ብቻ ነው፡፡ ምን አልባት አማራጭ ቢኖረኝ ኖሮ በእግዚአብሄር እምነት ባልተጉዋዝኩ ነበር፡፡ የእግዚአብሄርን አካሄዱን እና ሀይሉ፤ ባልተረዳሁ ነበር


ከባዱ ምንም ሳትበድለው የጎዳህን ሰው ከመሸሽ፤ ባህሪውን ለመረዳት መጣር ፈታኝ የሆነ የስነልቦና ተጽእኖም እንዳለው መረዳት ነበረብኝ፡፡  ቢሆንም ግን በዚህ መልኩ  ለማወቅ ቀጠልኩ፡፡አንድ ግዜ  የጠቀምኩዋት ሴት ግን የእኔን በጎ ነገር እንደማትወድ በተደጋጋሜ ያረጋገጥኩት ሴት፤ ለምን እንዲህ እንደምትከታተለኝ   ያደረኩትን  የእራሴን የህይወት የማትረፍ ምርምሬን ተመልከቱ፡፡ ድንገት አንድ ቀን እንደሚስጥር አድርጌ ኢህአዴግ መሆኔን አጫወትኩዋት፡፡ 
 እኔ ግን እንኩዋን ኢህአዴግ ልሆን ቀርቶ ምንም ፖለቲካ ውስጥ የለለሁ ሴት ነኝ፡፡ ግን እራሴን የሚረዳኝን የማወቅ ዘንባሌ በውስጤ አይሎብኛል፡፡ እሱዋም አንድ ሰሞን የኢህአዴግን ጥሩ ገጽታ በማውራት ከእኔ የበለጠች የኢህአዴግ ደጋፊ በመሆን  ድምጹዋን ከፍ አድርጋ፤ ኢህአዴግ ምንም ያላደረገን ድርጅት ነው፤ ጥሩ ነው፡፡ ልማት ነው  ምናምን እያለች  ወዲያው አንድ የተገናኘንበት ቦታ ላይ ማውራት ጀመረች፡፡  ነገሩ ገና ከኢህአዴግ ታገኛለች ብላ የፈራችውን ስልጣን ቀምታ ለመውሰድ መሆኑን ገብቶኛል፡፡ አንድ ሁለት ሴቶችንም በመጥራት  ኢህአዴግ ጥሩ ነው እያለች ቀጠለች፡፡ ያልገባት፤ ኢህአዴግ እሱ ያደራገውን እንጂ፤ ተደራጅተው የመጡትን፤ዝም ብሎ የሚቀበል አለመሆኑን የተረዳች አልመሰለኝም፡፤ አልያም መመርመሩ የማይቀር መሆኑን፡፡ በቃ እኔ ስለኢሕአዴግ ላወራ ስል አፌን በማለት ዋና አውራ ለመሆን እንዴት እንደጠራች ሳስበው፤ ሆዴ እጅግ ይስቃል፡፡ 

እንደቤተክርስቲያን ሳይሳለሙዋት የሚውሉም አጃቢዎቹዋ ለአንድ ሰሞን በዛው በእሱዋ አባባል ቀጠሉ፡፡ ከአንድ ወር በሁዋላ ያቺን የስልጣን ጥመኛ እና እኔን የምትከታተል ሴት፤    በናትሽ ይህ ግንቦት 7 የሚባል ድርጅት እንዴት አይነት ጥሩ ድርጅት መሰለሽ፤ በቅርቡ እኔን ሊያነጋግሩኝ ሳያስቡ የሚቀሩ አልመሰለኝም፡፡ ኢሳትም ኢንተርቪው ሊያደርገኝ እየሮጠ ነው አሉ አልኩዋት፡፡  ፊቱዋ በርበሬ ሲመስል አየው ነበር፡፡ እሱዋም ወዲያው፤ ስልክ ደዋውላ ታገኛለች ብላ የፈራቸውን  ሹመት ወደእሱዋ ለማዞር ይመስላል
እነዛን የከበቡዋትን ሚስኪኖች ሌክቸር ስታደርግ መዋሉዋን ሰማሁ፡፡ ወዲያውም ደግሞ ተቃዋሚ ሆና የሰበሰበቻቸውን ልጆች፤ አማራው እንዲህ ሆኖ እንዲያ ሆኖ፤ትግሬው ይህን አድርጎ ያን አድርጎ ስትል መዋሉዋ ገረመኝ፡፡  እውን ድጋፍም ጥፋትም የሚመጣው ከግለሰቦች መቀናናትም መሆኑን ያውቃሉ፡፡ ዘላቂነት ያለው ነገር መመስረት የማይቻልበት ብዙ ምክናያቶች ተመለከትኩ፡፡

 መደነጋገር የሚመጣው ከቅናት መሆኑን አየሁ እና ግርም ብሎኝ፤ ሌላ ቀን ፔንጤ እንዴት አይነት ጉደኛ እምነት መሰለሽ፤ እዛ ገብቼ የእርዳታ ነገር ለማቁዋቁዋም እጥራለሁ አልኩዋት፡፤ ወዲያው እከሌ እከሌ ፓስተር ቅርብ ወዳጁዋ መሆኑን አጫወተችኝ፡፡  እዛም የተሻለ ነገር እንድትሰራ እንደአማከሩዋት እና በቅርቡም እንደምተሰራ ተናገረች፡፡ በስሩዋ ያሉትንም ለአንድ ሰሞን እናንተ ጴንቴ ምን አደረጋችሁ፤ እና ፔንጤ ጋር መሰዳደብ የለብንም፡፡ እኔ ለምሳሌ ቤተክርስቲያናቸው ሄጃለሁ፤ የሚያስተምሩትም መሬት ጠብ አይለም በማለት ቀጠለች፡፡
መቼም እኒህ ሰዎች ከማርያም ንቅንቅ የማይሉ ሆኖባቸው እንጂ፤ በአንዲት ለሊት ፔንጤ አድርጋቸው ታድር ነበር፡፡ ማሪያም ግን ጴንጤ ጋር የለችም ብለው ስለሚያምኑ፤ ፔንጤን እንዳይቃወሙ ልታደርግ ትችላለች እንጂ ሌላውን መቀጥል እንደሚቸግራት አምናለሁ፡፡ ያም አልሆን እንደሚላት ስትረዳ
ፔንጤዎችንም እየተገናኘች፤ እኔን የሚያጣጥል፤ ከቶም ጠጪ ናት፤ ተደብቃ ትጠጣለች ማለቱዋን ሰማሁ፡፡ እንዳውም አንድ ወንድ፤ ባዩሽን የፈለግሽውን በያት፤ ግን እንኩዋን ልትጠጣ ቀርቶ ጠጪም
ትቃወማለች ሲል መመለሱን ሰማሁ፡፡ ፓስተሩ ሁሉ በእጄ ናቸው ስትል፤ ባዩሽ ቀድማኝ ፓስተር እንዳትሆን ያለች ይመስላል፡፡  ገረመኝ፡፡ ቅናት ማስተዋልን ይዘጋል እና፤ እኔን ለመጣል የምታደርገው ሁኔታ ሰውሮአታል እና፤ ሌላ ቀን  ግን  ማህበር አቁዋቁሜ የሚካኤልን ጸበል እንድንጠጣ ፤ አንዱዋን አንቺን አደርጋለሁ እና ምን ታስቢያለሽ አልኩዋት፡፡አስብበታለሁ ብላኝ ተለየን፡፡ በጣም የሚደንቀው አይንያወጣው ሁኔታ ግን   በሳምንቱ የሚካኤልን ማህበር kkkkkkk አቁዋቁዋመች፤ የሚገርመው እውነቱ የመሰከረልኝ እኔን ግን ነይ እስኪ ብላ አልጋበዘችኝም፡፡ እስኪ አሁን ምን ትሉታላችሁ ? ደሞ አንድ ቀን ሳገኛት አንድ ነገር አስቤአለሁ፡፡ እሱም ፕሬዝዳንት ኦባማ ሁዋይት ሃውስ ሊጋብዙኝ እንዳሰቡ፡፡  ኑሮ እንዲህ እያሉ የሚገፉ በሽ ናቸው፡፡ ግን ግርም የሚለኝ እንደልባቸው የሚያገለባብጡት  ተከታይ ግሩፕ መሰሪዎች ማፍራት መቻላቸው ነው፡፡
ወዳጄ ሆይ ፈራጅ ከሚያደርገው ዶሮ ወጥ  ለእውነት የቆመ ጠበቃ የሚያደርግህ ደረቅ እንጀራን ምረጥ፡፡
በቸር ባዩሽ  
 




Keine Kommentare:

Kommentar veröffentlichen